Quantcast
Channel: Zehabesha Amharic » Health
Viewing all 281 articles
Browse latest View live

Health: ባለትዳር መሆን የተሻለ ጤንነት እንዲኖረን ያደርጋል?

$
0
0

wedding copy

ባህላዊ ዕውቀትም ይሁን ዘመናዊ ሳይንስ ያገቡ ሰዎች ከወንደላጤዎች የተሻለ ረጅም ዕድሜ እና ጤንነት እንዳላቸው ይገልፃሉ፡፡

“ከላጤዎች ጋር ሲነፃፀር ባለትዳሮች ጤናማዎችና እና ለረጅም ዘመን ለመኖር የታደሉ ናቸው” ይላሉ በካሊፎርነያ ዩኒቨርስቲ ሳይኮሎጂስት የሆኑት ዶክተር ቴዎዶር ሮቤልስ፡፡ “ጥናቶች እንደሚያሳዩት ባለትዳሮች በተለይ ወንዶች ረዘም ላለ ዕድሜ ይኖራሉ፡፡ በልብ በሽታዎች የተነሳ የመሞት ዕድላቸው ከላጤዎች ሲተያይ ያነሰ ነው፡፡ ጤናማ ሰዎች ትዳር የመመስረት ፍላጎት አላቸው” በማለት ትዳር ጤናማ የማድረግ አቅም እንዳለው ይገልጻሉ፡፡
“የሚረዳዱና የሚተጋገዙ ጥንዶች ጤናማነታቸው ከግንኙነታቸው ጋር ተያያዥነት አለው” ይላሉ የኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ባልደረባዋ ዶክተር ጃኒስ ኪኮልት ግላሰር፡፡
ትዳር ለጤና በምክንያት
የጥሩ ባህርይ ባለቤት ያደርጋል

ጥንዶች በትዳር ሲጣመሩ በአደንዛዥ ዕፅ፣ በሲጋራ፣ እና በሌሎች ለጤና ጎጂ በሆኑ ነገሮች የሚደርሰባቸው ጉዳት እየቀነሰ ይሄዳል፡፡
“አብረው ለመኖር ሲስማው በፈቃደኝነትም ይሁን በትዳር አጣማሪያቸው ጉትጎታ ከነዚህ ሱሶች ስለሚታቀቡ ወይንም አወሳሰዳቸውን ስለሚቀንሱ የሚከሰት ነው” ይላሉ በኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሳይኮሎጂስት እና ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ክርስቶፈር ፍገንደስ፡፡

ማህበራዊ ግንኙነት

“ባለትዳር ከሆንክ/ሽ እስከ አሁን ከፈጠርካቸው/ ሻቸው ግንኙነቶች በጣም መቀራረብ የሠፈነበት እንደሆነ ትረዳለህ/ሽ፡፡ ይህ ማለት በማንኛውም ወቅት የምትፈልገውን/ጊውን እገዛ እና ድጋፍ ሊያደርግልህ/ ሽ የሚችል ሰው አለህ/ሽ ማለት ነው፡፡” ይላሉ ዶ/ር ጃኒስ፡፡
“በሌላ በኩል ደስተኛ ያልሆኑ ሰዎች ከማህበራዊ ኑሮ የተገለሉ ይሆናሉ፡፡ ይህም ወደ ድብርት ይመራቸዋል፡፡ የጤንነታቸውን ሁኔታም አይከታተሉም” ሲሉ በኒው ዮርክ ዩኒቨርሲቲ ሳይኪያትሪስት የሆኑት ዶክትር ሱዴፕታ ቫርማ ይናገራሉ፡፡

ጤናማ ልምዶችን ያዳብራሉ
ባለቤትዎ ጤናማ ልምዶችን እንዲያዳብሩ ሊረዱዎ ይችላሉ፡፡ “ባለቤትዎ በእርስዎ ባህርይ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡ ይህን መመገብ የለብህም/ሽም፤ አልኮል ቀንስ/ሺ ወዘተ የሚሉት ከዚህ በጎ ተፅዕኖ የሚመነጩ ናቸው” ይላሉ ዶክተር ቴዎዶር ሮቤልስ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በትዳራቸው ደስተኛ የሆኑ ሰዎች የዶክተሮቻቸውን ትዕዛዝ እንደሚያከብሩ አንድ ጥናት ይገልፃል፡፡
ከሚወዱት ሰው ጋር ለረጅም ጊዜ መኖርዎ ሌሎች የጤና ጠቀሜታዎችም አሉት፡፡ “አብዛኞቻችን ከፍቅረኞቻችን ጋር ለመዝናናት መኖራችን በጎ ጎን አለው፡፡ በትዳር ተጣምሮ መኖር ከሚያስገኘው ጋር ሲወዳደር ግን አነስተኛ ነው” ዶክተር ክርስቶፍር “ከትዳር የምናገኘው ፍቅርና መተጋገዝ ለራሳችን የምንሰጠውን እንክብካቤ እንዲጨምር ያደርጋል፡፡ ይህ የሚሆነው የትዳር ተጣማሪያችን በኛ ደስተኝነት ላይ የማይተካ ሚና ስላለው ነው” በማለት ዶክተር ቫርማ የትዳር ጥቅም ከፍተኛ እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡
ቀለበት ማጥለቅ ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ የተሻለ ትዳር ማለት የተሻለ ጤና ማለት ነው፡፡ የልብ ቀዶ ጥገና ከተደረገላቸው በሽተኞች ውስጥ በጥሩ ትዳር ውስጥ ያሉት የመዳን ዕድላቸው ከሌሎቹ የተሻለ እንደሆነ ከ15 ዓመታት በላይ የተካሄደ አንድ ጥናት ያስረዳል፡፡ ፍቅርና ደስታ በራቀው ትዳር ውስጥ የሚኖሩ በሽተኞች የመዳን እና በቶሎ የማገገም ዕድላቸው ዝቅተኛ እንደሆነም ጥናቱ ሳይጠቅስ አላለፈም፡፡

ለዚህ የተሰጠው ዋነኛ ምክንያት መጥፎ ትዳር ለከፍተኛ ጭንቀት የሚዳርግ በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የበሽታ መከላከል አቅምን ክፉኛ ያዳክማል፡፡ በተለየ ሴቶች ለዚህ ዓይነቱ ጭንቀት ተጋላጭ ናቸው፡፡ በትዳር ላይ በሚጋጥም ጥላቻ (ያለ መወደድ ስሜት) ሴቶቹ ስሜተ ስስ መሆናቸው ለችግር አጋልጧቸዋል
ይላሉ ዶክተር ጃኒስ፡፡

ዶክተር ጃኒስ እና የጥናት ቡድናቸው በምርመራክፍሎች ውስጥ ጥንዶች ባስቀመጡት ስውር ካሜራ ሲጨቃጨቁ ሁኔታውን በመቅረፅ ለማጥናት ሞክረዋል፡፡ “በክርክርና ባለመስማማት ወቅት ጥላቻን የሚያሳዩ ጥንዶች ጭንቀትን የሚያባብሱ ሆርሞኖች መጨመር ታይቶባቸዋል፡፡ የቃላት መቋሰሉ ከፈጠረው ህመም ለመዳንም ብዙ ጊዜ ይወስድባቸዋል” ብለዋል፡፡
ጠቅለል ተደርጐ ሲቀመጥ ከባድ የትዳር ችግር ያለባቸው ሰዎች የበሽታ መከላከል አቅም ሊዳከም ይችላል፡፡ የትዳር የጤናማነት ሁኔታ ወንዶችንም የጤና ችግር ሊያስከትልባቸው ይችላል፡፡

“በጥናታችን እንደደረስንበት ከሆነ ድብርት፣ አለቅጥ ክብደት መጨመር እና ከፍተኛ የደም ግፊት ደስተኛ ባልሆነ ትዳር ውስጥ በሚኖሩ ሴቶች ላይ ይታያሉ፡፡ ነገር ግን ወንዶች ትዳራቸው በሚፈጥርባቸው ብስጭት የአደንዛዥ ዕጾች ሱሰኛ ከሆኑ ተመሳሳይ የጤና ጉድለት ሊያገጥማቸው ይችላል” ሲሉ ዶክተር ቫርማ የችግሩን ስፋት ያስረዳሉ፡፡ እንደሳቸው እምነት ሁለቱም ፆታዎች ደስታ የራቀው ትዳር በሚያስከትላቸው አለመመቸቶች ይጠቃሉ፡፡ ይሁንና የሚያሳዩት የጉዳት መጠን ግን የተለያየ ነው፡፡
ብቸኞች

አንድ ሰው ብቸኛ (single) ነው ሲባል ከሌሎች ጋር የቅርብ ወዳጅነት መመስረት አይችልም ማለት አይደለም፡፡ ሌሎች ደግሞ ለፍቅር የሚሆናቸውን ሰው ባለማግኘታቸው ብቸኛ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለዚህ ዋነኛው መፍትሔ ጥሩ ጓደኞችን ማፍራት ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ሊያስቡልዎና ሊጠነቀቁልዎ እርስዎም ተመሳሳዩን ሊያደርጉላቸው ይችላሉ፡፡ ይህ ዓይነቱ ራስን በጥሩ ሰዎች መሃከል ማኖር ትዳራቸውን በፍቺ ለበተኑ ሰዎችም ይሠራል፡፡

ፍቺ ካለዕድሜ ከመሞት ጋር ተያያዥነት እንዳለውና በተለይ በወንዶች ላይ በስፋት እንደሚታይ የአሪዞና ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ዴቪድ ስባራ ይናገራሉ፡፡ “በዕድሜ በሰል ካሉ ሰዎች ውስጥ ከፍቺ በኋላ በደስታ የተሞላ ህይወት ሲመሩ የሚታዩ ይኖራሉ፡፡ ደስታ በራቀው ትዳር ውስጥ ካሉና ትዳርዎ እንዲሠራ የሚችሉትን ያህል ከለፉ በኋላ ተስፋ እንደሌለው ካወቁ ፍቺ ምክንያታዊና አምነን መቀበል ያለብን አማራጭ ይሆናል፡፡ ተፋትተው ደስተኛ ሆነው መኖር ከቻሉ ፍቺ የሚያመጣቸው ጐጂ ጐኖች ሊያሳስብዎ አይገቡም” ይላሉ ዶክተር ዴቪድ፡፡

ከፍቺ በኋላ ሴቶች ከወንዶች በተሻለ መልኩ ጥሩ ስሜት ሊሰማቸው ይችላል፡፡ “ላጤዎችን እና የጤናቸውን ሁኔታ ስናይ ሴቶቹ ከወንዶቹ በተሻለ ጤንነት ላይ ይገኛሉ፡፡” የሚሉት ዶክተር ክርስቶፈር ባለትዳሮች ወይንም አብረው የሚኖሩ ፍቅረኞች ለመስማማት በማይችሉበት ወቅት በአክብሮት ያለ ዘለፋ እንዲነጋገሩ ይመከራል፡፡ ጥላቻ በከፍተኛ ሁኔታ የሚንፀባረቅበት ክርክርና ጭቅጭቅ ለጤና ጉዳት ያጋልጣል፡፡ በተገቢው ሁኔታ መነጋገር ሲባል ማዳመጥ፣ መስጠት፣ ቅድሚያ መስጠት እና የተናጋሪውን ስሜት መረዳትን ያጠቃልላል፡፡ በሰው ልጆች ውስጥ ያለው ትልቁ ፍላጐት ለመወደድ መንሰፍሰፍ ሲሆን እውቅና ማግኘት ደግሞ ሌላው ነው፡፡ ይህን ካደረጉ “እያዳመጥኩህ/ሽ ነው” የሚል መልዕክት ያስተላልፋሉ፡፡ ይህ አይነቱ መተሳሰብ የትዳር ችግሮቻችሁን በቀላሉ ለመፍታት እና ለመስማማት ያስችላችኋል፡፡

ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ታትሞ ወጥቶ ነበር


የአሳ ክትፎ አሰራር (Video)

$
0
0

መልክ በጉሮሮ ይገባል ይባላል:: ጤናማ ምግብ መመገብ ጤናማ ያደርጋል:: አሳ ለጤና ያለውን ጠቀሜታ ከዚህ ቀደም ብዙ ጊዜ አስተምረናል:: ዛሬ ደግሞ የአሳ ክትፎ አሰራርን አቅርበንላችኋል:: የ እህትቻንን ትምህርት በቭድዮ ተከታተሉት::

የአሳ ክትፎ አሰራር (Video)

Health: ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ 5 የስኳር ሕመም ምልክቶች

$
0
0

suger
(በዶክተር ሆነሊያት ኤፍሬም)
የስኳር ሕመምን በተመለከተ በተለያዩ የጤና ምክር መስጫ ፕሮግራሞች ላይ ሰፋ ያለ ግንዛቤ የማስጨበቻ ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው፡፡
ከዚህ በታች ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ የሕመሙን ጠቋሚ ምልክቶች እንግራችኋለሁ፡፡ ስለስኳር ሕመም በዝርዝር በቅርቡ የሚያስገባችሁ ይሆናል፡፡
1) ከተለመደው ጊዜ በተለይ ውሃ መጠማትና በተደጋጋሚ የውኃ ሽንት መምጣት፡፡
የስኳር ሕመም ለኩላሊት ችግር በማጋለጥ ቀዳሚ ደረጃን የሚይዝ ሲሁን በደምውስጥ የሚገኝ የስኳር መጠን መጨመር የኩላሊት ሥራ ያዛባል፡፡
2) የድካም ስሜት መሰማት
የስኳር ሕመም ከፍተኛ የድካም ስሜትን ያስከትላል፡፡ የሰውንት ክብደት መጨመር በራሱ ለስኳር ሕመም ከማጋለጥ ባለፈ የድካም ስሜት እንዲበረታ ያደርጋል፡፡
3) የዓይን ችግር
ማናኛውም ዓይነት የዓይን ችግር የስኳር ሕመም ምልክት ሊሆን ስለሚችል ጊዜ ሳይሰጡ ወደ ሕክምና ቦታ በመሄድ ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
የስኳር ሕመምተኞች ለግላውኮማ የመጋለጥ ዕድላቸው ስለሚጨምርና በካታራክት (በዓይን ሞራ) ሊጠቁ ስለሚችሉ የዓይን ሕመም ከተሰማ ወደ ሕክምና ቦታ መሄድ ይመከራል፡፡
4) የእግር መደንዘዝ
የስኳር ሕመም የነርቭ ጉዳትን ያስከትላል፡፡ ይህም ጉዳት በአብዛኛው የሚከሰተው በእጃችንና በእግራችን ላይ ባሉ ነርቮች ላይ ነው፡፡ በነርቭ ወይንም በደም ሥር ላይ የሚደርስ ጉዳት የእግር መደንዘዝ ቀጥሎም የሕመም ስሜትን ያስከትላል፡፡ ሕመሙ በጊዜ ብዛት እየባሰ የሚሄድ ሲሆን መጠጥ እና ሲጋር ማጨስ ሕመሙን ያባብሰዋል፡፡
5) የቆዳ ላይ ኢንፌክሽንና በቶሎ የማይድን ቁስለት
የስኳር ሕመም ቆዳችንን ጨምሮ ማንኛውንም የሰውነት ክፍላችንን ሊጎዳ ይችላል እንዲያውም የስኳር ሕመም ያለበት ሰው በቀላሉ በባክቴሪያ እና በፈንገስ የሚመጣ ለቆዳ ላይ ኢንፌክሽን ያጋልጣል እነዚህም ኢንፌክሽኖች ቁስለትን ያስከትላሉ በቶሎ ሊድኑም አይችሉም፡፡
ጤና ይስጥልኝ

Health: የጥቁር አዝሙድ አስደናቂ የጤና በረከቶች

$
0
0

Black cumin
በሙለታ መንገሻ

ሰዎች ጥቁር አዝሙድን ለበርካታ ዓመታት ከተለያዩ ህመሞች ለመፈወስ ይጠቀሙበታል።

ጥቁር አዝሙድ በሞቃታማ አካባቢዎች የሚበቅል ተክል ሲሆን፥ በጥንት የስልጣኔ ዘመን ግብጾች እንደ አለርጂ፣ የሰውነት መመረዝ፣ ድብርት እና በርከት ያሉ የጤና ችግሮችን ለማከም ሲጠቀሙበት እንደነበረ ይነገርለታል።

ከሞት በቀር ሁሉንም በሽታ የሚያድን ተክል እስከማለት የሚነገርለት ጥቁር አዝሙድ ከዳቦ ጋር ቀላቅሎ መጋገርም የሚመከር ሲሆን፥ ይህም የሆድ ህመም፣ የሳንባ እንዲሁም ማስመለስን ለማስቆም ይረዳልም ይባላል።

ጥቁር አዝሙድ

ጥቁር አዝሙድ የሆዳችን ተግባር እንዲስተካከል በማድረግ የምግብ መፈጨት ስርዓትን ያፋጥናል።

እንዲሁም ከመተንፈሻ አካላት ጋር ተያይዘው የሚከሰቱ እንደ አስም፣ ብሮንካይት እና ሌሎች ህመሞችን ለማከም ይረዳል።

በሽታ የመከላከል አቅማችንን በመጨመር እንደ ካንሰር ባሉ ህመሞች በቀላሉ እንዳንጋለጥም ይረዳናል።

የጥቁር አዝሙድ ዘይት

የጥቁር አዝሙድ ዘይት ለጤና በጣም ጠቃሚ ከሚባሉት ውስጥ ይመደባል።

ይህም እንደ ብሮንካይት፣ አስም እና ማይግሬይን የራስ ህመምን ለማከም እንደሚረዳ ይነገርለታል።

እንዲሁም የጸጉር መነቃቀልን የሚከላከል ሲሆን፥ ክብደትን ለመጨመር ለሚፈልጉም ጠቃሚ ነው ተብሏል።

በተጨማሪም የስኳር ህመምን ለማከም፣ እና የደም ግፊትን ለመቆጣጠር የሚረዳን ሲሆን፥ ችግሩ ያለባቸው ሰዎች ቢያንስ ለተከታታይ 6 ወራት ያህል በሚመገቡት ምግብ ውስጥ የጥቁር አዝሙድ ዘይት ጨምረው እንዲመገቡ ይመከራል።

የጥቁር አዝሙድ ዘይቱን በምግባችን ውስጥ በምንጨምርበት ጊዜም ምግቡን አብስለን ከጨረሰን በኋላ መጨመር ይኖርብናል።

ሌሎች በሽታዎችን ለመከላከል ይረዳን ዘንድም በቀን ለሶስት ጊዜ አንድ የሻይ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት መጠጣት ይመከራል።

አስምን ለማከም የሚረዳን የጥቁር አዝሙድ ሽሮፕ

አንድ የሻይ ማንኪያ ጥቁር አዝሙድ በደንብ እንዲደቅ አድርገን መውቀጥ፣ ሁለት ፍሬ ነጭ ስንኩርት የተፈጨ፣ ሁለት የሻይ ማንኪያ ማር አንድ ላይ በመደባለቅ፤ ውህዱን ሁሌም ጠዋት ከእንቅልፋችን እንደነቃን ከምግብ በፊት መጠጣት።

ምንጭ፦ yourhealthypage.com

Health: የድድ ህመምና መፍትሔዎቹ

$
0
0

Dede Tirs

ማለዳ ወደ ሥራ ለመምጣት በገባሁበት ታክሲ ውስጥ ነው ከፊቴ የተቀመጡት ሁለት ጓደኛሞች የሚነጋገሩት ነገር ጆሮዬ ውስጥ የገባው። «ጥርሶቼ ደህና ሆነው ድዴን ያመኛል ስፍቀው በጣም ይደማል ምን ይሻለኛል?» ትላለች የመጀመሪያዋ «በሎሚ እሺው ይተውሻል ጥርስሽ ደህና ከሆነ ችግር የለውም» የሚል መልስ ሰጠቻት አብራት ያለች የዕደሜ አቻዋ። የእነርሱን ወሬ ተወት አድርጌ ወደ ራሴ ሃሳብ ገባሁ። «እውነት የድድ ህመም በቀላል የምናየው ነው ወይስ ከባድ በሽታ?» ስል አሰብኩ። የዚህን ጥያቄ መልስ ለማግኘት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥርስ ህክምና ማዕከል ውስጥ የማስተማርና የህክምና አገልግሎት የሚሰጡትን ዶክተር ባንቺአምላክ ደምሴ ለማግኘት ቀጠሮ ያዝኩ።

ረዳት ፕሮፌሰር ዶክተር ባንቺአምላክ የፊትና የአገጭ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስትና መምህርት ናቸው። ስለተነሳሁበት ጉዳይ ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተውኛልና ላካፍላችሁ ወደድኩ። ለቃለምልሱ ፈቃደኛ ስለሆኑና እውቀታቸውን ስላካፈሉን  ምስጋናዬ በቅድሚያ ይድረሳቸው።

– የድድ ህመም ምንድንነውመንስኤውስ?

ዶክተር ባንቺአምላክ፦ የድድ ህመም ሲባል የአንድ በሽታ ስም ቢመስልም የተለያየ ዓይነት የድድ ህመሞች አሉ። አንደኛው በኢንፌክሽን ምክንያት የሚመጣ ማለትም በምንበላው ምግብ የተነሳ የመቆጣት ህመም ሲሆን፤ ሌላው ደግሞ በእባጭ መልክ የሚመጣ ከጥርስ ጋር በተያያዘ ከዕጢ ወይም ከካንሰር ጋር በተያያዘ የሚመጣ የድድ ህመም ነው። ሌላው ከሰውነታችን የጤንነት ጉድለት ማለትም በቪታሚን ሲ እጥረት ምክንያት በስኳር በሽታና ሌሎች የጤና ችግሮች ሳቢያ ሊመጣ የሚችል ነው። በዋናነት በእድገት አለመስተካከል ማለትም ጥርስ እድገቱን ሳይጨርስ ውስጥ ሲቀር የሚከሰተውና በጥርስ ንፅህና ጉድለት የሚመጡት ናቸው። በተለይ ደግሞ በጥርስ ንፅሀና ጉድለት የሚከሰተው ህመም በአብዛኛው የሀገራችን ታማሚዎች ችግር ነው።

አዲስ ዘመን፦ ህመሙ የሚያመጣው ጉዳት እንዴት ይገለጻል?

ዶክተር ባንቺአምላክ፦ በጥርስ ንፅህና ጉድለት የሚመጣው በሽታ የድድ መሸሽ እና ድድ አቅም አጥቶ ጥርስ በራሱ ጊዜ እንዲወልቅ ያደርጋል፡፡ ሌላው ደግሞ እንደየ ህመሙ ዓይነት የተለያዩ ጉዳቶችን በማድረስ የነርቭ ችግር እስከማምጣት ብሎም እስከሞት የሚያደርሱ የድድ ህመሞች መገለጫዎች ናቸው።

 ይሄን ችግር ለመከላከል ምን መደረግ አለበት?

ዶክተር ባንቺአምላክ፦ የሀገራችን ዋንኛ ችግር የሆነውን በፅዳት ጉድለት የሚመጣ የጥርስ ህመም በአግባቡ በማፅዳት ብቻ መከላከል ይቻላል። ይህም ሲባል በመጀመሪያ ደረጃ በመጉመጥመጥ፣ በመፋቂያ በመፋቅ ማስወገድ ይቻላል፡፡ አንዳንዴም እየተመገብናቸው ቆጠሻሻን የሚያስወግዱ የምግብ ዓይነቶች ማለትም እንደ ሸንኮራ፣ ኮክ፣ ካሮት የመሳሰሉትን በማኘክ ማፅዳት ይቻላል። ሌላው በጥርስ ሳሙና መቦረሽ ፅዳትን ይፈጥራል። 

ሌሎቹን ዓይነት ህመሞችንስ በምን መከላከል እንችላለን?

ዶክተር ባንቺ አምላክ፦ ሌሎቹን ማለትም በተለያዩ ህመሞች ምክንያት የሚመጡትን መከላከል በጣም ከባድ ነው። ለምሳሌ ኤችአይ.ቪ ህመም ያለባቸው ሰዎች ድዳቸው የማበጥ ችግር ያመጣል፡፡ ለተለያዩ ዓይነት በሽታዎች የሚወሰዷቸው መድኃኒቶችም ድድን ሊያሳብጡ ይችላሉ። በእርግዝና ወቅት የሚመጡ የድድ ህመሞች አሉ። እነዚህን በህክምና ለማስወገድ መሞከርና በራሳቸው ጊዜ ሊተዉ የሚችሉ ከመሆናቸው በቀር ይህ ቢደረግ ይተዋል የሚባል ነገር አይኖርም።

 ድድ ራሱ አብጦ ራሱ ይጎድላል ይሄስ ህመም ነው ወይስ ሌላ የጤና ችግር?

ዶክተር ባንቺአምላክ፦ ይህ ችግር የሚመጣው «ሸሄላ» ማለትም ምግብ በጥርስ ውስጡ ተጠራቅሞ በሚጠነክርበት ጊዜ በድድ ውስጥ ስር ሰዶ ድዱ እንዲቆጣና እንዲደማ ሲያደርገው ነው፡፡ ይሄ ጥርስ እየተፀዳም ቢሆን በአጸዳድ ጉድለት ሊመጣ ይችላል፡፡ በነገራችን ላይ በጥርስ ህክምና ታሪክ እንደ ድድ ህመም ከባድና አስቸጋሪ ሁኔታ የለም። ድድን ማዳን ከባድ ነው። ጥርሱን አቃፊ አልባ ሊያደርግ የሚችል ጉዳት ያደርሳል።

 ድድ የማበጥ ችግር እንዳ ይከሰትበ ት ምን መደረግ አለበት?

ዶክተር ባንቺ አምላክ፦ ችግሩ እንዳይመጣ መንስኤውን ማቆም ዋናው መፍትሔ ነው። በበሽታ ምክንያት የሚመጣውንም የድድ ህመም በመታከም በትክክለኛ አፋፋቅ በማፅዳት የጥርስ ህመምን ማስወገድ ይኖርብናል። ንፁህ ጥርስ እንዲኖረንም ቢያነስ በቀን ሁለቴ ማለትም ጠዋት ቁርስ ከተበላ በኋላና ማታ ወደ መኝታ ከመኬዱ በፊት ጥርስ መፋቅ አለበት። ውሃ መጉመጥመጥም ለጥርስ ንፅህና ይረዳል።

ጥርስ ሲፋቅ ቢያንስ ለደቂቃ ያህል በትዕግስት መፋቅ አለበት። ይህም ከቀኝ የላይኛው የጥርስ ክፍል እየተፋቀ ወደ ግራ ከግራ ደግሞ ወደታችኛው የጥርስ ክፍል ከዚያ ደግሞ ወደቀኝ በማድረግ ውስጡንና ምላስንም በጥንቃቄና በተገቢው መንገድ ማፅዳት ያስፈልጋል።

የድድ ህክምናስ እንዴት ይካሄዳል?

ዶክተር ባንቺ፦ ህክምናው በንፅህና ጉድለት የሚመጣውን በንፅህና ከመከላከል ባሻገር ህክምናው የተጋገረ ቆሻሻ ካለ በእጥበት ማስወገድ፣ የተጎዳ ጥርስ ካለ በሙሌት ማከም ወይንም መንቀል፣ ድድ በተለያዩ መድኃኒቶች እንዲድን ማድረግና እስከ ቀዶ ህክምና የሚደርሱ የህክምና ዓይነቶች አሉት።

 የጥርስ ሳሙና መጠቀም አፍ ያሸታል የሚባለውስ ነገር ምን ያህል እውነት ነው?

ዶክተር ባንቺአምላክ፦ አዎ ብዙ ሰው አፍ ያሸታል ሲል ይደመጣል። የጥርስ ብሩሽ በመጠቀም አፍ ያሸታል የሚባለው ነገር ግን ከእውነት የራቀ ነው። እንዲያውም በተቃራኒው ለአፍ ጥሩ ጠረን በመስጠት ጥሩ ስሜት እንዲሰማን ያደርጋል። ማንኛውም የጥርስ ሳሙና የማፅዳት፣ የአፍ ጠረንን የማሳመር አቅም አለው፣ ተዋስያንን የመግደል ብቃትም አለው፣ ፍሎራይድ የያዘ ስለሚሆን መጠቀሙ ምንም ጉዳት አይኖረውም። 

በአጋጣሚ አለርጂክ ኖሯቸው የድድ መቆጣትና ሌላ ችግር እንዳይገጥማቸው የሚመቻቸውን መምረጥ የተጠቃሚዎች ፈንታ ነው። አፍ ያሸታል የሚባለው ነገር የሚመጣው እኔ ሲመስለኝ ንፅህናውን ተለማምደው ሲተውት የሚከተለው የቆሻሻውን የመለየት ሂደት ሊሆን ይችላል።

የምንጠቀመውሰ የጥርስ ብሩሽ ለምን ያህል ጊዜ ያገለግላል?

ዶክተር ባንቺ አምላክ፦ በአብዛኛው የጥርስ ብሩሽ አጠቃቀም ላይ ችግሮች ይስተዋላሉ። የምንጠቀመው የጥርስ ብሩሽ የእጅ መያዣው ወደታች ብሩሹን ወደላይ በማድረግ አየር እንዲያገኝ ማድረግ ይቻላል። በየሦስት ወሩ በመቀየር ጤናው በተጠበቀ ብሩሽ ጥርስን ማፅዳት ተገቢ ነው።

የጥርስ ሳሙና በራሱ የጣፋጭነት ጣዕም ስላለው ጣፋጭነቱ ጥርስን አይጎዳም ወይ?

ዶክተር ባንቺ አምላክ፦ የጥርስ ሳሙናዎች ሲዘጋጁ ጣዕም ለማሳመር የሚደረጉ ፍሌቨሮች ካልሆኑ በስተቀር ጥርስን የሚጎዳ ምንም ነገር አይኖረውም፡፡ ይህማ ከሆነ የተነሱለትን ዓላማ ዘነጉ ማለት ነው። የጥርስ ሳሙናዎች ጥርስ የማጠንከር የአፍ ጠረንን የማሳመርና የማፅዳት አቅም ነው ያሏቸው።

በአጠቃላይ በድድ ላይ ያሉትን ህመሞች ከማከም በላይ ለሁሉም ቢያንስ በቀን ሁለቴ ማፅዳት፣ ጥርስ ስለታመመ ብቻ ሳይሆን በየጊዜው እየሄዱ የጥርሱ ህመም ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ማሳየት፣ ከመታመሙና ችግር ከመፈጠሩ በፊት መከላከል ያስችላል። 

ጸሐፊ አስመረት ብስራት

Health: ጂም መሥራት ያቆሙ ሰዎች ውፍረትን የሚከላከሉባቸው 10 ብልሃቶች!!

$
0
0

በአንድ ወቅት ጥሩ አድርገን የገነባነውን የሰውነት ቅርፅና ወደምንፈልገው ደረጃ ያመጣነውን ክብደት እንዲሁም ጤናችንን በቶሎ እንዳናጣ የተለያዩ አማራጮችን መከተል ያስፈልጋል፡፡

ባለሙያዎች በዚህ ረገድ እንቅስቃሴ በማቆም ላይ ለሚገኙት መፍትሄ ያሉትን በየጊዜው ይፋ ያደርጋሉ፡፡ እነዚህ ምክሮች እንቅስቃሴን በስንፍና ለማቆም ለወሰኑ ብዙ አይፈይዱም ብለዋል የምክሩ ባለቤቶች፡፡
gym
ወደ አካላዊ እንቅስቃሴ እንዲገቡ ከሚጠየቁ ሰዎች የሚሰማ የተለመደ ምላሽ ነው፡፡ ‹‹የእንቅስቃሴ ጥቅሙ ምንድነው? በሆነ አጋጣሚ ያቆምኩ ዕለት መወፈሬ እንደሁ አይቀር?›› የሚል፡፡ እነዚህ ሰዎች የህይወታቸው አንዱ አካል አድርገው እስካልተረዱት ድረስ ወደ እንቅስቃሴ እንዲገቡ ቀድሞም አይመከርም፡፡ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ሰዎች ስፖርት መሥራት ባቆሙ ከ8ኛው ሳምንት ጀምሮ እንደገና መወፈር የሚጀምሩ ሲሆን ለዚህ መሰሉ ማቆምም የሚገደዱባቸው ሁለት ምክንያቶች ጊዜ ማጣትና የአካል ጉዳት ናቸው ተብሏል፡፡ እንቅስቃሴ ስናቆም ለግርሻ ክብደት እንዳንጋለጥም ልንከተላቸው የሚገቡ ስልቶች ምንድን ናቸው? 10 ጠቃሚ አማራጮችን ይዘናል፡፡

1. በዚህ ረገድ እጅግ መሰረታዊ የተባለው፣ እንቅስቃሴ ሲቆም በምንወስደው የካሎሪ መጠን ላይ ከፍተኛ ቅናሽ ማድረግ ነው፡፡ መደበኛውና የወትሮ እንቅስቃሴ ሲቆም ከፍተኛ ክብደት መከተሉ እርግጥ ነው፡፡ ለሚሊዮኖች ዝቅተኛ የአመጋገብ አማራጭ ሲቀርብላቸው ደስተኞች ባለመሆናቸው እንቅስቃሴን ካቆሙ በኋላ በቀላሉ ለማይገላገሉት ክብደት የሚጋለጡትም ለዚሁ ነው፡፡ ነገር ግን አመጋገብን (በተለይ ከፍተኛ የካሎሪ መጠን ያላቸው) በመቀነስ ብቻ ይሄንን ልናሳካ እንችላለን፡፡ ስፖርቱ ውስጥ ባለን ጊዜ ወደ ሰውነታችን ስናስገባ የቆየነው የካሎሪ መጠን፣ በእንቅስቃሴ አማካኝነት የመቃጠል እድል ስላለው ጉዳቱ ዝቅተኛ ይሆን ነበር፡፡ በአንፃሩ እንቅስቃሴው ሲቆምና የምግብ ፍጆታችን የማይቀንስ ከሆነ፣ የማይቃጠል ከፍተኛ የካሎሪን መጠን በሰውነታችን ውስጥ በማከማቸት (የቅባት ኢንቬንተሪ) ለውፍረትና ውፍረት አመጣሽ ችግሮች ያጋልጠናል፡፡

2. በተቻለ መጠንና ባገኘነው አጋጣሚ (እንደ መደበኛው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እርካታ ባይሰጥም) እዛም እዚህም መራመዱና ዕቃዎችን ማንሳትና ማውረዱ፣ ሰውነታችን እንዲሰራና ድብርትም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሊቀንስልን ይችላል፡፡ ድብርት እንቅስቃሴን በሚያቆሙ ሰዎች መካከል የተለመደ ችግር ነው፡፡ እናም መራመዱና አነስተኛ የቤት እንቅስቃሴዎች ማድረጉ ረዥም ጊዜ ተቀምጦ ከማሳለፍ እንድንቆጠብ ያደርገናል፡፡

3. በስራ እና በሌሎች ፕሮግራሞች ጊዜአችን የተጣበበ ከሆነ፣ በሳምንት አንድ ወይም ሁለት ጊዜ የክብደት እንቅስቃሴዎችን በማከናወን፣ ለረዥም ጊዜ የገነባነውን የቱንቻ ጥንካሬ እና ቅርፅ በነበረበት ማቆየት እንችላለን፡፡ ይሄንን ሳያቋርጡ በመቀጠል ጊዜው ሲፈቅድ ደግሞ ወደ መደበኛው ልምምድ መግባት ይቻላል፡፡ በየሁለት ሳምንቱ የሚደረገው ይህ ስፖርታዊ ልምምድ ለረጅም ጊዜ መቆየት እንደሌለበት መረዳት ያስፈልጋል፡፡ በቶሎ ወደ መደበኛ ልምምዶች ለመግባት ሁኔታዎችን ማመቻቸት ይኖርብናል፡፡

4. እንቅስቃሴ ለማቋረጥ ያስገደደን የጊዜ እጥረት ከሆነ ቀደም ሲል ይደረግ የነበረውን ልምምድ ጊዜ በግማሽ ለማሳጠር ሁኔታዎችን ማመቻቸት ሌላው አማራጭ ነው፡፡ የኤሮቢክስ ስፖርት ተመራማሪዎች፣ ልምምዱን በግማሽ ወደ ማሳጠር ስንገባ የቀድሞውን የእንቅስቃሴ መጠን እና ጥንካሬ በዚህ ጊዜ እንድንሸፍን ይመክሩናል፡፡

5. የቤት ውስጥ ሥራ መሸፈን፡- ቤትና ግቢ ማፅዳት፣ ልጆችን መንከባከብ፣ ማብሰል እና ሌሎች የቤት ውስጥ የሥራ ድርሻዎች እንቅስቃሴን ካቆምን በኋላ የእኛ የሥራ ድርሻ እንዲሆኑ ማድረግ ጥቅሙ ለራስ ነው፡፡ የሚገዙ ዕቃዎች ሲኖሩም ነቃ ብሎ መሳተፍ ነው፡፡

6. በሥራም ሆነ ያለ ሥራ ወደ ትላልቅ ህንፃዎች በመሄድ፣ ደረጃዎችን ወደ ላይ እና ታች ማለት ጥሩ አማራጭ ነው፡፡ በተለይ በዚህ አጋጣሚ መደበኛ እንቅስቃሴ ማድረግ ላልቻሉት ይሄ ተመራጭ መፍትሄ ይመስላል፡፡

7. ሰውነታችን ክብደታችንን ለመቀነስ እንደ መሳሪያ መጠቀም እንችላለን፡፡ በተለይ የቤት እንቅስቃሴዎች የሚባሉትን ፑሽ አፕ ፑል አፕ፣ ቁጭ ብድግ፣ እግርን እና አንገትን የሚያፍታቱትን ጠዋት ከእንቅልፋችን ስንነቃና ማታም ልንተኛ ስንዘጋጅ መስራት ይኖርብናል ይላሉ ባለሙያዎቹ፡፡ እነዚህ በቀላሉ ባለንበት ቦታ ሆነን ልንተገብራቸው የሚችሉ ነገር ግን ውጤት የሚያመጡ ናቸው፡፡

8. ቴሌቪዥንና ኮምፒውተር ላይ የምናሳልፈውን ጊዜ መቀነስ ይኖርብናል፡፡ ይሄ ከመደበኛው እንቅስቃሴ በተለያዩ ምክንያቶች ስንገለል ልንከተላቸው ከሚገቡ አማራጮች መካከል ነው፡፡ ለረዥም ጊዜ መቀመጥን የሚያስገድዱ ተግባሮችም በዚህ ውስጥ ይካተታሉ፡፡ እናም በጥንቃቄ እንቅስቃሴዎች ይተኳቸው፡፡

9. ልምምድ በምናደርግበት ወቅት ከእንቅልፋችን ከምንነሳበት 20 እና 30 ደቂቃዎች ቀድመን መንቃት ይኖርብናል፡፡ ይሄ ተግባራችን ሰውነታችን የሚንቀሳቀስበትን የጊዜ ርዝመት በማስፋት፣ ያቆምነውን የስፖርት ልምምድ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንድናካክስ ይረዳናል፡፡

10. በጊዜ እጥረት ምክንያት ከልምምድ ልንርቅ ከሆነ የተሻለ የሚባለው፣ አጭር እና ውጤታማ በሚባል የሰውነት እንቅስቃሴዎች መሸፈን ላይ ትኩረት ማድረግን አለመዘንጋት ነው፡፡ ይሄም ቢያንስ የ10 ደቂቃ እንቅስቃሴን በቀን ከሁለት እስከ ሶስት ጊዜ ማከናወን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ጊዜአችንን በሚገባ ማስተዳደር የሚጠይቅ መመሪያ ነው፡፡ ሆኖም ካላስፈላጊ የግርሻ ክብደት ይገላግላል ይጠቀሙበት መልካም ጤንነት!

Health: ወጣት ልጆችዎን በክትባት ይጠብቁ!

$
0
0

Zehebasha 7-15

Minnesota Department of Health (MDH)

ወጣት ልጆችም ክትባት እንደሚያስፈልጋቸው ያውቃሉን? ልጆች እያደጉ በሄዱ ቁጥር፣ በልጅነታቸው የወሰዱዋቸው ክትባቶች በሽታ የመከላከል ብቃት መዳከም ይጀምራል። በተጨማሪ ወጣት ልጆች በዚህ የህይወት ዘመናቸው ሊያጣቋቸው የሚችሉ ኣዳዲስ በሽታዎች ኣሉ። የልጆችዎን ጤንነት በቲዳፕ (Tdap)፣ መኒንጎኮካል (meningococcal)፣ ኤች.ፒ.ቪ. (HPV)፣ እና ኢንፍሉዌንዛ ክትባቶች ኣማካኝነት ይጠብቁ።

የወጣት ልጆች ክትባቶች

Tdap ክትባት

ይህ ክትባት ከሶስት ከባድ በሽታዎች ይከላከላል፦ መንጋጋ ቆልፍ (tetanus)፣ ዲፍተሪኣ (diphtheria)፣እና ፐርቱሲስ (እንዲሁም ትክትክ በመባል ይታወቃል)። ወጣት ልጅዎ ቲዳፕ ክትባት 11 ወይም 12 ዓመት ሲሞላው መውሰድ አለበት።

መኒጎኮካል ክትባት (MCV4)

መኒንጎኮካል ኮንጁጌት ክትባት፣ እንደዚሁም የMCV4 ክትባት በመባል የሚታወቅ፣ ማጅራት ገትር በሽታ ጠንቅ ሊሆኑ ከሚችሉ የተወሰኑ ጀርሞች ይከላከል። ማጅራት ገትር በጭንቅላት ሽፋን እና የጀርባ ኣጥንት ላይ እብጠት ሊያስከትል የሚችል ከባድ በሽታ ነው። እንዲሁም ለሂወት ኣዳጋች የሆነ የደም ኢንፌክሽን ሊያስከትል ይችላል። ልጅዎ ይህንን ክትባት መውሰድ የሚያስፈልገው 11 ወይ 12 ዓመት ሲሞላው ነው። 16 ዓመት ሲሞላቸው ኣንድ የመኒንጎኮካል ክትባት ያስፈልጋቸዋል።

HPV ቫክሲን

ይህ ክትባት የካንሰር መከላከያ ነው። በአብዛኛው ሁሉም ሰው በሂወት ዘመኑ የተወሰነ ወቅት ላይ ለ HPV ኢንፌክሽን ይጋለጣል እንዲሁም የተወሰኑ የ HPV ዓይነቶች የካንሰር ጠንቅ ሊሆኑ ይችላሉ። HPV ክትባት ከHPV ኢንፌክሽን እና ከሚያስከትሉት ካንሰር ለመከላከል ይጠቅማሉ። ወንዶችም ሆኑ ሴቶች የ HPV ክትባት መውሰድ ይጠበቅባቸዋል። ወጣት ልጆች 11 ወይም 12 ዓመት ሲሞላቸው ሶስት ተከታታይ የ HPV ክትባት መውሰድ አለባቸው።

የኢንፍሉዌንዛ ክትባት

ይህ ክትባት ከኢንፍሉዌንዛ (ጉንፋን) የሚከላከል ሲሆን ሁሌ በፎል/መፀው ወቅት መሰጠት አለበት። ኢንፍሉዌንዛ የውስጥ ሰውነት ፈሳሽ ማጠር ወይም የሳምባ ኢንፌክሽን የመሳሰሉ የጤና ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል።

ክትባት አስፈሪ መሆን የለበትም!

ወጣት ልጅዎ ክትባቶቹን በሚወስዱበት ጊዜ በተቻለ መጠን አንዲረጋጉና ዘና እንዲሉ በማድረግ ይርዱዋቸው። የሚወዷቸውን ሙዚቃዎቻቸውና ሄድፎኖቻቸው ይዘው እንዲመጡ ያድርጉ፤ ወይም አይናቸውን ጨፍነው ስለሚወዱት ቦታ ወይም ጨዋታ እንዲያስቡ ያድርጉ። ክትባት መውሰድ በትንሹ ሊያሳምም እንደሚችል ሆኖም ግን ከመታመም በጣም እንደሚሻል ያስታውሷቸው።

ልጄ መከተብ ያለበት መቼ ነው?

እነዚህ ክትባቶች ለመውሰድ ኣመቺው ጊዜ ዓመታዊ ምርመራ በሚደረግበት ወቅት ነው። በተጨማሪ ለስፖርት፣ ለትምህርት ቤት፣ ወይም ለካምፕ አስፈላጊ የሆነውን የሰውነት ምርመራ በሚደረግበት ወቅት ልጅዎ እነዚህ ክትባቶችን መውሰድ ይችላል። ምንም እንኳን ወጣት ልጅዎ 11 ወይም 12 ዓመት በሞላው ወቅት እነዚህን ክትባቶች ሳይወስዳቸው ቢቀርም፣ አሁንም ቢሆን ከፍ ባለ ዕድሜ ላይ ሆኖም መውሰድ ይችላል። ከሀኪምዎ ጋር በሚገናኙበት እያንዳንዱ ወቅት ላይ ልጅዎ መውሰድ ስላለበት ክትባቶች መጠየቅ የሚደገፍ ሀሳብ ነው።

ስለነዚህ ክትባቶች ሌላ ማወቅ ያለብኝ ነገር ምንድን ነው?

እነዚህ ክትባቶች በሙሉ በጥንቃቄ የተጠኑ እና ደህንነታቸው የተጠበቀና ውጤታማ ናቸው። ክትባት በተሰጠበት የሰውነት ክፍል ቀለል ያለ የህመም ስሜትና መቅላትን የመሳሰሉ የጎንዮሽ ጉዳቶች ሊያስከትሉ ይችላሉ። አልፎ አልፎ ደግሞ ወጣት ልጆች ክትባት ከወሰዱ በኋላ ነፍሳቸው ሊስቱ ይችላሉ። ክትባት ከወሰዱ በኋላ ለ 15 ደቂቃ ማረፍ የሚደገፍ ሃሳብ ነው። ወጣት ልጅዎ ከባድ አለርጂ ያለው ከሆነ ማንኛውም ዓይነት ክትባቶት ከመውሰዱ በፊት ለኪምዎ ይጠቁሙ።

የእነዚህን ክትባቶች ወጪ የሚሸፍን እርዳታ እንዴት ማግኘት እችላለሁ?

ክትባት ለልጆች (Vaccines for Children) (VFC) ፕሮግራም ለአንዳንድ ህጻናት እና ወጣት ልጆች ነጻ ወይም ዋጋቸው ርካሽ የሆኑ ክትባቶችን ያቀርባል። ይህን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት እና ብቁ መሆንዎት ወይም አለመሆንዎት ለማወቅ ሀኪምዎን ያነጋግሩ።

ተጨማሪ መረጃ ከየት ማግኘት እችላለሁ?

የልጅዎን ጤንነት እና ደስተኛነት ለማስጠበቅ የሚረዳ የበለጠ መረጃ ለማግኘት www.vax4teens.com የሚለውን ድረ-ገጽ ይጎብኙ።

Health: በዕርግዝና ወቅት ወሲባዊ ግንኙነቱ በምን መልኩ ሊቀጥል ይገባል?

$
0
0

እርግዝና እና ወሲብ
እስከየት ድረስ

በእርግዝና ወቅት ስለ ወሲብ ማሰብ ለነብሰጡር ሴቶች የመጨረሻው ከባድ ተግባር ሊሆን ይችላል፡፡ በተለይ በማቅለሽለሽ እና በማስመለስ እንዲሁም ድካም በሚበረታበት በዚህ ወቅት አንዳንድ ሴቶች የወሲባዊ ግንኙነት ፍላጎታቸው ሊቀስቅስ ይችላል፡፡ የወንድ ተጣማሪያቸውም በተመሳሳይ አንዳንዶች ግንኙነቱ ስሜትን በማስቀደም ብቻ ሊፈፅሙት ሲነሳሱ ሌሎቹ ወንዶች በአንፃሩ ህፃኑን እና ነብሰጡር ወዳጆቻቸውን ላለመጉዳት በማሰብ ወሲባዊ ግንኙነትን በዚህ ወቅት በእጅጉ የሚፈሩት ተግባር ይሆናል፡፡ አልጋ ለይቶ የማደር ሃሳቡ የሚመነጨውም ለዚሁ ሊሆን ይችላል፡፡ በአሜሪካ ኖርዝ ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ አሶሽየት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ዳይና ሳለሰች ‹‹በእርግዝና ወቅት ወሲባዊ ግንኙነት ማድረግ ጥሩም መጥፎም ዜና ይዞ የሚመጣ ሊሆን ይችላል›› ይላሉ፡፡ የሴቶቹ እርግዝና ያልተወሳሰበ መሆን እና ዝቅተኛ አደጋ የሚያስከትል መሆኑ ሲረጋገጥ እንዲሁም የተጓዳኞች የግል አተያይ መሰረታዊ መሆኑን ከግምት እንድናስገባ ይመክሩናል፡፡ አንዳንዶች በዚህ ወቅት ወሲብን ይበልጥ ሲያጣጥሙት ሌሎች ደግሞ ዝቅተኛው የደስታ ምንጭ አድርገው ይወስዱታል፡፡
Premature Ejaculation 1
በመጀመሪያዎቹ የእርግዝና ወቅቶች ማለትም ሴቶች የማጥወልወል እና የድካሙ ስሜት ውስጥ ሲሆኑ ብዙዎቹ ከፍተኛ ወሲብ ፍላጎት አያሳዩም ነው ባለሙያዋ የሚሉት፡፡ በሁለተኛው ዙር የእርግዝና ወቅት ደግሞ በአንፃራዊነት የተሻለ የሚባል ስሜት ውስጥ ይገባሉ፡፡ በተለይ የመራቢያ አካላቸው ላይ በተለየ ሁኔታ የሚመነጨው ዘይትም ለወሲባዊ ግንኙነት ይበልጥ እንዲሳቡ ምክንያት ይሆናል ባይ ናቸው፡፡ በዚህ ወቅት ነብሰጡር ሴቶች ከወሲባዊ ግንኙነት ብዙ እንዲርቁ ከሚያደርጋቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ ደግሞ ሆዳቸው በዚህ ጊዜ ሙሉ ለሙሉ የክብ ቅርፅ የሚይዝ በመሆኑ ነው፡፡ ይሄ በሶስተኛው የእርግዝና ዘርፍ የሚጠበቅ አይደለም፡፡

ሆድ ሲገፋ እንዲሁም ድካምም በእጅጉ ሲበረታ የወሲብ ስሜቱ በዛው ልክ እየቀዘቀዘ ይመጣል፡፡

ዶ/ር ሳላሰች እንደሚሉት ባለቤት የፍቅር ጓደኛ ወደ መጨረሻዎቹ ወራት እየተቃረበች ከመጣችው ከነብሰጡር ጓደኛ ጋር ወንዱ ወሲባዊ ግንኙነት የማድረግ ፍላጎቱ ከተነሳሳ ብዙ መጨነቅ አይገባም ይላሉ፡፡ በእንቁላሉ በሚገባ የተከለለ በመሆኑ ህፃኑ በምንም መልኩ ለአደጋ የተጋለጠ ሊሆን አይችልም እና፡፡ ባለሙያዎች ሴቶች በእርግዝና ምክንያት ለውጥ ውስጥ ሲያልፉ ለትዳር አጋራቸው አሁንም ያልበረደ ፍቅር እንዳላቸው ማሳየት፣ እርስ በርስ የመግባባት መስመሩም በተሻለ መንገድ እንዲቀጥል ማድረግ ይኖርባቸዋል ይላሉ፡፡

በዕርግዝና ወቅት ወሲባዊ ግንኙነቱ በምን መልኩ ሊቀጥል ይገባል?

ሴቷ የእርግዝና ወቅቷ እየጨመረ እና ሆዷም እየገፋ ሲመጣ ባህላዊና የተለመደው ወሲባዊ ቅርፅ ማለትም ወንዱ ከላይ የመሆን አቅጣጫ ምቾት የሚሰጣት አይሆንም፡፡ በዚህ ምክንያት ሳልስቼን ጨምሮ የዘርፉ ባለሙያዎች ከመሀል ወይም ፊት ለፊት የመተኛት የግንኙነት አቅጣጫዎችን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ ያስገነዝባሉ፡፡ ከዚያ ባለፈ ባሎቻቸው በጀርባቸው እንደተኙ አጠቃላይ የወሲባዊ ግንኙነትን ሂደት ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር በሚችሉበት አቅጣጫ ማለትም ከላይ እንዲሆኑ ይመከራል፡፡

በተወሰኑ ደረጃዎችም ነብሰጡር ሴቶች በጀርባቸው ብዙ እንዳይተኙ ይመከራሉ፡፡ ምክንያቱም የለብ ምት እና የደም ግፊትን ሊያስከትሉባት የሚችሉት ሰፓይን የሀይፐርቴንሲቭ ሲለንድሮምን ያስከትላልና፡፡ ችግሩ በተለይ ሴቷ በሶስተኛው እርግዝና እርከን ላይ ስትገኝ ይበልጥ የከፋ የመሆን ዕድል አለው፡፡
በግንኙነት ወቅት ምንም አይነት ችግር የማይገጥማት እናት ያለ ችግር በሂደቱ መቀጠል ትችላለች፡፡ ነገር ግን ከወሲብ በኋላ መድማትና ሌሎች ህመሞች የሚከተሉ ከሆነ የቀይ መስመሩ እየታለፈ ስለመሆኑ ማሳያ ነው እና በአፋጣኝ የህክምና ዶክተሮችን ማማከሩ ተገቢ ነው፡፡ ነብሰጡር ሴቶች በመሰል ግንኙነት ወቅት በትልቁ ትኩረት ይሰጡበት ዘንድ ባለሙዎች ከሚያስጠነቅቁት ሁኔታ መካከል አንዱ በወሲባዊ ግንኙነት ወቅት በሚተላለፉ በሽታዎች የተጠቃ የትዳር አጋር ካላቸው ኮንዶምን ጨምሮ ሌሎች መከላከያ መንገዶችን በወሲባዊ ግንኙነት ወቅት እንዲጠቀሙ ነው፡፡
ባለሙያዋ ዶ/ር ሆፍማን በፆታዊ ግንኙነት ወቅት ነብሰጡር ሴቶች በተቻለ መጠን ሰውነታቸውን ማዳመጥ እና ከጓደኛ ጋር ግልፅ የመሆንን አስፈላጊነት ያሰምሩበታል፡፡

በሌላ መልኩ ነብሰጡር እናቶች በወሲባዊ ግንኙነት ወቅት ሊያገረሹ የሚችሉ ኢንፌክሽኖች ተጋላጭ የመሆን ስጋት ካለባቸውና የተቃራኒ ፆታ አጋራቸው ትብብርም የሚፈልጉትን ያህል ካልሆነ በራሳቸው የሌቴክስ የሴቶች ኮንዶምን በግንኙነት ወቅት መጠቀም እንደሚኖርባቸው ዶ/ር ሆፍማን ያስገነዝባሉ፡፡ ሌቴክስ ኮንዶሞች ውጤታማ ካልሆኑ ደግሞ ሌሎች የሴት ኮንዶሞችን መሞከር ጠቃሚ ነው፡፡
ደጋግመው ሁሉም ባለሙያዎች የሚያሳስቡት በወሲባዊ ግንኙነት ወቅት ምቾት የሚነሱ ሁኔታዎች ነብሰጡር ሴቶች ሲገጥማቸው በተቻለ መጠን ለተጣማሪያቸው ወዲያው ማሳወቅ ያለባቸው መሆኑን ነው፡፡ የወሲብ ስሜቱ ቢኖር እና በሌላ መልኩ በተለመደው መልኩ ግንኙነቱን ማድረግ አስቸጋሪ ከሆነ ደግሞ ሌሎች የስሜት መቆጣጠሪያና ኤሮቲክ ተግባራትን ማጤን ይመከራል፡፡ ከወሲብ እኩል ስሜታችንን ልናቀዘቅዝባቸው የምንችላቸው እንደ መሳሳም፣ መተቃቀፍ፣ እና መተሳሰቡ በራሱ የተሻሉ መፍትሄዎች ናቸው፡፡
ወሲባዊ ግንኙነት በእርግዝና ወራትም የሚቀጥል ተፈጥሯዊ ጉዳይ ነው፡፡ ባለሙያዎቹም ደጋግመው ጤናማ እርግዝና የሚያሳልፉ ሴቶች መሰል ግንኙነት በራሳቸውም ሆነ በተሸከሙት ልጅ ላይ ሊከሰት የሚችል ችግር አይኖርም፡፡ በተፈጥሮ መጠበቂያ ግንቦች በሚገባ የተከለለ በመሆኑ፡፡
አንዳንዶቹ የህክምና ባለሙያዎች ነብሰጡሮች ወሲባዊ ግንኙነትን በመጨረሻዎቹ የእርግዝና ወራት እንዲያስወግዱ ይመክራሉ፡፡ ሊከሰት የሚችለውን ችግር በሚገባ በማስረዳት ረገድ ርቀው መሄድ ባይችሉም፡፡

በእርግዝና ወቅት ወሲባዊ ግንኙነትን እንድናስወግድ የሚያስገድዱ ምክንያቶች
ሐኪሞች ከዚህ በታች የተዘረዘሩና በእርግዝና ላይ አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ችግሮች ካሉብሽ ወሲብን እንዳትፈፅሚ ሊከለክልሽ ይችላል፡፡
– የመራቢያ አካል ላይ የሚከሰት የመድማት ችግር ካለብሽ
– መንታ አልያም ከሁለት በላይ ልጆችን እንደምትወልጂ ተነግሮሽ በዛ መሰረት የመውለጃ ጊዜሽን እየጠበቅሽ ከሆነ (ከ37 ሳምንታት በፊት) የመውለድ ስጋት እና ታሪክ ካለሽ
– የማህፀንሽ በር ያለ ጊዜ የመለጠጥ እና የመከፈት ምልክት የሚያሳይ ከሆነ…

ልጅሽን ከወለድሽ በኋላ መቼ ነው ወደ ግንኙነት መመለስ ያለብሽ?
ልጅሽን በተፈጥሮ መንገድ፣ በቀዶ ጥገናና ወይም በሌላ የህክምና እርዳታ ከወለድሽ በኋላ ሰውነትሽ ስለሚዳከም ለማገገምና ወደ መደበኛው የወሲብ ህይወት ለመመለስ ጊዜ መውሰድ ይኖርብሻል፡፡ ብዙዎቹ የጤና ባለሙያዎች ከወሊድ በኋላ ሴቶች በትንሹ እስከ 6 ሳምንት ከመሰል ግንኙነት መታቀብ አለባቸው በሚለው የጊዜ መመሪያ ላይ ይስማማሉ፡፡ የጊዜ ገደቡ ሴቷ የማህፀን በሯ ወደ ቀድሞ ቦታው እንዲመለስ ቁስሎችም እንዲሽሩ ይረዳል፡፡
ወደ መደበኛ ወሲባዊ ህይወትሽ ስትመለሺ ግንኙነቱን ቀስ ብለሽ መጀመር ይኖርብሻል፡፡ ያልተፈለገ እርግዝናን እና ኢንፌክሽኖችን እንዲሁም የአባላዘር በሽታዎች የመጠቃት እድሉ አሁንም ያለብሽ እንደሆነም መድሐኒቶችን እና መከላከያዎችን መጠቀም ይኖርብሻል፡፡


Health: ለመልካም ትዳር 7 መልካም የንግግር ጥበቦች

$
0
0

sad couple

ባልና ሚስት ተፋቅረው እንደተጋቡ አንዳቸው ለአንዳቸው እምነት እንዳላቸው ያስባሉ፡፡ ስለዚህም አንዱ ለአንዱ መልካም ባል ወይም ሚስት መሆኑንን ወይም መሆኗን የትዳር አጋሩ ወይም አጋሯ እንደሚያምኑ ስለሚታሰብ ያንን በአንድም በሌላም መልዕክቶች ውስጥ ማረጋገጥ ይፈልጋሉ

ሚስት ትጠይቃለች፥«ጉዳዩን ጨረስክ?»

ባል «ጨርሻለሁ»

«መፅሃፉን የት አደረግከው»

«መደርደሪያው ላይ አለ»

«ዛሬ አንድ ጉዳይ ነበረኝ ልጆቹን ከትምህርት ቤት ብታመጣቸው»

«እኔም አይመቸኝም»

ድርቅ ያለ ንግግር፣ የፍቅር ቅመም የጎደላቸው ቃላት፣ ወዳጃዊ ያልሆኑ አቀራረቦች::

የእናንተንስ ጎጆ ከስሩ ታውቃላችሁ? የመጠላላት የመኮራረፍ ያለመረዳዳት ያለመተጋገዝ የስልቸታ ሁሉ

ምንጩ የምትነጋገሩበት አግባብ፣ የምትነጋገሩበት ጊዜ፣ የምትነጋገሩበት ስሜትና የመሳሰሉት ተደማምረው የትዳራችሁን ደስታ ይነጥቃሉ ይላሉ የጋብቻን ጉዳይ የሚመረምሩ ምሁራን፡፡ በአነጋገር ስሜቶች ያለመጣጣም ደስተኛ ወዳልሆነ የትዳር ጎጆ ይመራል፡፡ መልካም ያልሆነ የንግግርና የስሜት አለመጣጣምም ለረጅም ግብ የታሰበውን ትዳር መራር ያደርጋል፡፡ በአንዳንድ ወዳጆቻችሁ ቤት ጎራ ትሉ ይሆናል፡፡ በቤቱ ወስጥ የሰው ህይወት የሌላ እስኪመሰል ድረስ በሚያስፈራ የፀጥታ ድባብ ተውጦ በባልና ሚስቱ ዘንድ ያለው የንግግርና የስሜት መራራቅ እንደተራራ ገዝፎ አይታችሁት ይሆናል፡፡ ድርቅ ያለና ጣዕም የሌለው ንግግር፣ ግዴለሽናትና ስልቸታን የተሞላ ምልልስ ትሰማላችሁ፡፡ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ፊት ለፊት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ጀርባ በሁለቱ መካከል ያለው የንግግርና የስሜት መጣጣም ጥያቄ ውስጥ መግባቱን ታያላችሁ፡፡

የግንኙነት ክህሎት በትዳር ውስጥ ወሳኝ ሚና አለው፡፡ ብዙ የሥነልቡና ሊቃውንትም በዚህ ይስማማሉ፡፡ መቼም ትዳር ሲባል በሁለት ሰዎች ማለትም በወንድና ሴት መሀል ለዘላቂ ሕይወት የሚደረግ ተፈጥሮን መሠረት ያደረ ጥልቅ ግንኙነት ነው፡፡ በመሆኑም በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሐሳብ፣ መረጃ፣ ስሜትን እና የመሳሰሉትን ለኑሮአቸው የሚበጁ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ላይ በየዕለቱና በየሰዓቱ በቃል፣ በጽሑፍ ወይም በምልክት መልእክትን ይለዋወጣሉ፡፡ ግንኙነት ሲባልም ሁልጊዜም ታሳቢ የሚሆኑት መልእክት ሰጨው፣ መልእክት ተቀባዩና መልእክት ማድረሻ ምህዋር፣ በዚያ ላይ ተጽዕኖ የሚሳድሩ እንቅፋቶችና ግብረ መልሶች ናቸው፡፡

የትዳር አጋሮች አንዱ ለአንዱ በሚኖራቸው ግንኙነት ውስጥ መልእክትን ማለትም ሊያስተላልፉ የፈለጉት የሐሳብ፣ የስሜት ወይም የመረጃ ይዘትን ይመለከታል፡፡ በትዳር ውስጥ ለአጋራችን የምናስተላልፈው መልእክት ይዘት በትዳራችን ላይ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል፡፡ ለፍሬያማ ግንኙነት ግን በምናስተላልፋቸው መልእክቶች ይዘት ምን መምሰል እንዳለባቸው የሚሠጡ አንዳንድ ምክሮችን ማስታወስ ይበጃል፡፡

7. የሚያበረታታ መልእክት

የትዳር አጋራችን ሊሰማው የሚመኘው የሚያስደስተውንና የሚጠብቀውን መልእክት ቢሆን መልካም ነው፡፡ ባልና ሚስት ተፋቅረው እንደተጋቡ አንዳቸው ለአንዳቸው እምነት እንዳላቸው ያስባሉ፡፡ ስለዚህም አንዱ ለአንዱ መልካም ባል ወይም ሚስት መሆኑንን ወይም መሆኗን የትዳር አጋሩ ወይም አጋሯ እንደሚያምኑ ስለሚታሰብ ያንን በአንድም በሌላም መልእክቶች ውስጥ ማረጋገጥ ይፈልጋሉ፡፡ እርሱን በማግባቷ ወይም በማግባቱ ደስተኛ መሆኗን/መሆኑን/ የሚገልጽ መልእክት ትዳርን የሚያንጽ ነው፡፡ በትዳር ውስጥ በራስ መተማመንን ያሳድጋል፡፡ ተዘውትሮ የሚታይ የመተቸት ዝንባሌ ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ በቀጣዮቹ የትዳር ጊዜያት ላይ መተማመንን ያሳጣል፡፡ ተስፋ መቁረጥ ያስከትላል፡፡

አንድ ቢሊ የሚባል ሰው ናስቲ ስለተባለች ሚስቱ የግንኙነት ዘይቤ ሲናገር ያለው የምሬት ቃሉን ላስታውሳችሁ ‹‹ሚስቴ ሁሉን ነገር ማጥቂያ ታደርገዋለች፡፡ አነጋገሯ የሚያበሳጭና ለቁጣ የሚጋብዝ ነው፤ ለምን እንዲህ ማድረግ አልቻልክም? ለምን ይሄን አላደረግህም? ወዘተ በሚሉ ጥያቄዎች ልትጀምረው ትችላለች፤ ቃላቶቿ ብቻ አይደሉም የምትናገርበት ድምፀት ችግር ያለበት ነው፤ ናስቲ የማታከብርና በሁሉም ሁኔታ ውስጥ ስህተት ፈላጊ ነች፡፡ ለምን እንዲህ ታደርጊያለሽ ስላት ያነሳሁትን ሐሳቤን ለማስቀየር ትጥራለች፤ ወዲያው ሌላ ስህተት ትሰራለች፤ ለዓመታት ያ ሆኖብናል፡፡ በችግሯ ላይ መወያየትንም ትቃወማለች፡፡ ስለዚህ ብወዳትም በዚህ ግንኙነት መንፈስ ከእርሷ ጋር መቆየት አልቻልኩም፤ በዚህ ጊዜ የፍቺ ጥያቄ ሳቀርብላት አላቅማማችም ምክንያቱም ስሕተት ሠራሁ ብላ አሁንም አታስብምና፡፡›› ብሏል፡፡

አንዳንዴ ትችት ብቻ ሳይሆን ሁሌ ተቃራኒ የመሆን ፍላጎቶችን ማሳየትም አንዱ የማያበረታታ ግንኙነት ነው፡፡ ሰማዩ ሰማየዊ ሆኖ ሳለ ሰማየዊ ሰማይ ነው ስትል አይ ዳመና አለው እያሉ በነገር ሁሉ ለመቃረን መሞከርም ዝንባሌው የግንኙነት እንቅፋት ነው፡፡

6. ገርነት ለመልካም ግንኙነት

እንዲህ ያሉ የሚያበረታቱ መልእክቶች ደግሞ የሰመረ የመልእክት ምህዋር በሆኑ መልካምና ልባዊነቱን በሚያመለክቱ አቀራረቦች ሲተላለፉ ለመልእክት ተቀባዩ የተረዳና የሚያረካ ይሆናል፡፡ ለመልካምም ግብረ መልስ ይጋብዛል፡፡ ከመልካም አቀራረብ ጋር አያይዘን የምናነሳቸው ተያያዥ የሆኑ የሚከተሉትን በጎ ልማዶችን መያዝ ጠቃሚ ነው፡፡ የመጀመሪያው ገርነት ነው፡፡ ኃይለኛ፣ ሸካራና ግትር መሆንን ከመሳሰሉ ለትዳር ጠንቅ የሆኑ ልማዶችን ማስወገድ ማለት ነው፡፡ እነዚህ ጠንቆች ካሉ ከትዳር አጋር የሚወጡ መልእክቶች የሚያበረታቱ ሳይሆኑ በትችት የተሞሉ፣ አስቆጪና ተስፋ አስቆራጭ መልእክቶች ይሆናሉ፡፡

ትችት ግንኙነትን ይመርዛል፡፡ ከእያንዳንዱ ቃል ጀርባ ሐሳብ አለ፡፡ የትችት ቃላት የሚይዙት መልእክት ደግሞ የሚያበረታታ አይሆንም፡፡ ነገር ግን በገርነት ውስጥ ግንኙነትን የሚመሩ ሰዎች ለትዳራቸውና ትዳራቸውን የሚያንጽ ትችት በመሰንዘር አጋራቸውን በሚያበረታታ መንገድ መልእክት ያስተላልፋሉ፡፡

Unhappy woman lying in couchUnhappy woman lying in couch

5. ንቁ አዳማጭነት ለመልካም ግንኙነት

የሚያበረታታ መልእክት ለማስተላለፍም ይሁን ለመቀበል ብቁና ንቁ ሆኖ የትዳር አጋርን ለመስማት/ለማዳመጥ/ መዘጋጀት ያሻል፡፡ የትዳር አጋሮች መልእክት በሚያስተላልፉ ጊዜ ሁሉ በንቃት ጆሮን መስጠት ማክበርን፣ ትኩረት መስጠትን ያመለክታል፡፡ ይህ የበለጠ የሚገለጸው የትዳር አጋር መልእክት ሲያስተላልፍ በቀጥታ ወደ እርሱ እያዩ መልእክት በመቀበል፣ ሌላ የሚፈጽሙት ጉዳይ ካለ ከትዳር አጋር በላይ እንዳልሆነ በሚገልጽ አግባብ ለጊዜው ተወት አድርጎ ለመስማት መሻትን በማሳየት ነው፡፡ ከተቻለም አክብሮ የትዳር አጋርን መልእክት በጉጉት ለመስማት መቻልን ለማረጋገጥ በቃላት ወይም በመልእክት በሚገለጽ ግብረ መልስ ማጀብ ብልህነት ነው፡፡

ማደመጥ የትዳር አጋር በሚስቱ ወይም በባሏ ዘንድ ዋጋ እንደሚሰጠው እንዲያስብ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ማዳመጥ የሰመረ ግንኙነትና ክብካቤ ማሳያም ነው፡፡ ለራሳቸው ብቻ እንደሚያወሩ የሚሰማቸው ከሆነ ከትዳር አጋራቸው ያገኙት አንዳችም ነገር እንደሌለ በማሰብ፣ ከዚህ ወይም ከዚህች ሰው ጋር የመኖሩ አስፈላጊነት ምንድነው ብለው እንዲጠይቁ ሊያደርግ ይችላል፡፡

4. ለጠንካራ ጎን እውቅና መስጠት

ከዚህ በተጨማሪ በሚተላለፉ መልእክቶች ውስጥ የሚያበረታታ መልክ እንዲይዝ የሚያስችለው ሌላው ነገር ጠንካራ ጎኖችን ወይም የትዳር አጋር ያገኛቸውን/ያገኘችውን ስኬት በጉልህና በተደጋጋሚ መግለጽና እውቅና መስጠት ነው፡፡ አንዳንዶች በድክመታቸውም ለመማር ለመታነጽ ዝግጁ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ጠንካራው ሲነገራቸው የሚያውቁትን ደካማ ጎን ለማስተካከል እስኪችሉ ብርታት ያገኛሉ፡፡ አንዳንዶች ደግሞ የማያውቁትን ያላስተዋሉትን ደካማ ጎናቸውን በትዳር አጋራቸው እንዲነገራቸው እስኪጋብዙ ድረስ ፈቃደኝነት ሊታይባቸው ይችላል፡፡

3. የቃላት ኃይል በግንኙነት ውስጥ

ቃላት ያማሉ፤ ይፈውሳሉም፡፡ በትዳር ውስጥ ያላቸው ሚና እንዲሁ ነው፡፡ ትዳርን ያፈርሳሉ ወይም ያንጻሉ፡፡ የስድብ፣ የመመካት፣ የትምክህት፣ የሚያስቆጣ፣ የሽሙጥ፣ የምጸት፣ የጥርጣሬ፣ የቂም በቀል፣ የአድልዎ፣ የሚያገሉ፣ ወዘተ ቃላት እጅግ አደገኛና በትዳር ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያላቸው ናቸው፡፡ የርህራሄ፣ የፍቅር፣ የተስፋ፣ የሚያጽናና፣ የስኬት፣ የማክበር፣ የትህትና፣ የምስጋና፣ የግልጽነት፣ የይቅርታ ወዘተ ቃላት ደግሞ ትዳርን እጅግ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያንጹ ናቸው፡፡ ስለዚህ ባለትዳሮች አንዳቸው ለአንዳቸው የሚነጋገሩበትን ቃላት በግዴለሽነት ሳይሆን በጥንቃቄ በጭካኔ ሳይሆን በርህራሄ መንፈስ ከልባቸው መዝገብ አውጥተው መናገር ይገባቸዋል፡፡

በተለይ ከትዳር አጋር ጋር ወይም ከሌላ አካል ጋር በተፈጠረ አለመስማማት ውስጥ የሚነገሩ ቃላት በዘላቂ ግንኙነት ውስጥ የማይረሱ ጠባሳዎች ጥለው እንዳይቀሩ ቃላትን መርጦ በትዕግስት ውስጥ ሆኖ ራስን ተቆጣጥሮ መናገር አስፈላጊ ይሆናል፡፡ በትዳር ውስጥ የሚያጋጩ ነገሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ምክንያታዊ የሆኑና ከቁጥጥር ውጪ የማይወጡ ግጭቶች መራር ቃላትን ሊያስተናግዱ አይችሉም፡፡ በአንጻሩ ግን ሆን ተብሎ ተዘውትሮ የሚፈጸም ምክንያታዊ ያልሆነ ወይም ከልኩ በላይ የሆነ የቃላት ጦርነትና ስሜታዊ በቃላት የሚፈጸም ረገጣ ውሎ አድሮ ትዳርን ለጥፋት ይዳርጋል፡፡

ቃላት ከፍተኛ ሐሳብን የተሸከሙ በመሆኑ በንግግራችን አንድን የትዳር አጋር አካልና መንፈስ የሚጎዳ መዘዝ ሊያመጣ ይችላል፡፡ ብዙ የሕመም ዓይነቶች ሊተክሉ ይችላሉ፡፡ በርካቶች ከአጋሮቻቸው የተነገሩ ቃላትን እያሰቡ ምን ሊለኝ /ልትለኝ/ ፈልጎ ነው እያሉ ሲተረጉሙ የሚውሉ፣ ለምን እንዲህ ብዬ መልስ አልሰጠሁም የሚል የበቀልን የቁጭት ሐሳብ ተሸክመው የሚውሉ የሚያድሩ፣ ወዘተ ጊዜያቸውን የሚጨርሱ፣ ለሥራ ያላቸውን ትኩረት በማጣት ባዝነው የሚውሉ፣ ከረጅምና ተከታታይ ጭንቀት የተነሳም ለአእምሮና አካላዊ ህመም የሚዳርጉ በርካታ ሰዎች አሉ፡፡

በአንጻሩ ደግሞ የአጋሮቻቸው የሚያበረታቱ ቃላት ከፍተኛ የመንፈስ ጥንካሬ የሚሠጣቸውና ስኬት በስኬት የሚሆኑ፣ ፍቅራቸውም ከጊዜ ጊዜ የሚጨምርባቸው በርካታ ሰዎችም ይኖራሉ፡፡

2. ዐውድን ያገናዘበ የቃላት ልውውጥ

ባለትዳሮች በሰዎች ፊት ሲወያዩና ለብቻቸው ሆነው ሲወያዩ የሚኖረው ዐውድ ሊለያይ ይችላል፡፡ በሰዎች ፊት ሲወያዩ የሚቀባበሉአቸው ቃላት በጥንቃቄ የተሞሉና የፍቅርና መከባበር መንፈስ በተሞላበት ሁኔታ እንዲሆን ይፈልጋሉ፡፡ በሰዎች ፊት ሆነው ሲያወሩ ሊሰሟቸው የሚፈልጉአቸውና የማይፈልጓቸው ቃላት ይኖራሉ፡፡ ለብቻ ሆነው ሲወያዩ የሚነጋገሩባቸውን ቃላት መጠቀም ለአንዳንዶች ሊያስቆጣቸው ይችላል፡፡ ወይም አያስደስታቸው ይሆናል፡፡ በዚያም ምክንያት የትዳር አጋራቸውን በሰው ፊት ይዘው መቅረብ የማይፈልጉ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ በሌላ አንጻር ሁኔታዎችን ከግምት ያስገቡ የንግግር ቃላትን መጠቀም የሚችሉ፣ የትዳር አጋሮቻቸውን በማንም ፊት ይዘው ቢቀርቡ የማያፍሩ ምናልባትም ከትዳር አጋር ጋር ሆኖ መታደም ኩራት የሚፈጥርላቸውም በርካቶች ይኖራሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ችግርን ለመፍታት በሚደረጉ በአንዳንድ ጥብቅ ጉዳዮች ላይ ከተቻለም ለችግሮች መፍትሔ ለመስጠት የሚደረጉ ውይይቶች የሚደረጉበትን ጊዜና ሁኔታ መምረጥ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ የትዳር አጋር በሌሎች ምክንያቶች ተቆጥቶ ሳለ ተበሳጭቶ ሳለ ወይም ተርቦ እያለ ቸኩሎ እያለ… ትኩረትና እርጋታ የሚፈልጉ ጉዳዮችን አንስቶ ለመነጋገር መሞከር በግንኙነት ሂደቱ ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በሌሎች ሰዎች ፊት ሲሆኑ የትዳር አጋሮቻቸው እስከሚገረሙ ድረስ ደስ የሚያሰኙ ማራኪ ቃላትን የሚጠቀሙ ሰዎች ወደቤቶቻቸው ሲገቡ ተለውጠው ለትዳር አጋር እንደኮሶ የሚመሩ ቃላትን የሚያዘንቡም ይኖራሉ፡፡ እንዲህ ያሉት በልማዳዊ ንግግሮች ‹‹የውጪ አልጋ የቤት ቀጋ›› የሚባለው ዓይነት አቀራረብ ያላቸው ናቸው፡፡ በውጪ ምስጉንና የመልካም ቃላት ባለቤት ሆነው ሳለ በቤት ግን ትዳራቸውን ለማነጽ በማይጠቅሙ ኃላፊነት የጎደላቸው ንግግሮች የሚታጀቡ ይኖራሉ፡፡

1. የይቅርታ ኃይል በግንኙነት ክህሎት

ግንኙነት ሁልጊዜ የሰመረ ላይሆን ይችላል እንኳን ትዳርን በመሰለ የረጅም ዘመናት ተቋም ቀርቶ በየዕለት አጋጣሚዎቻችን በሚኖረን የሥራ፣ የንግድ፣ የማህበራዊ ኑሮ፣ ወዘተ ግንኙነት ውስጥ ታግሰን ልናልፋቸው ያልቻልናቸው ያልተሳኩ ግንኙነቶች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ የግንኙነት እንቅፋቶች ከምንጠቀምባቸው የቃላት ጥራት፣ ከመልእክቱ ተቀባይ ግንዛቤ እጥረት፣ ወይም ከመስሚያና መናገሪያ አካላችን ችግር ጋር በተያያዘ ሳይሰሙ ወይም በደንብ ሳይናገሩ በሚፈጠር የግልጽነት ችግር የሚያጋጥሙ የግንኙነት እንቅፋቶች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ነገሮች በትዳር ውስጥ ባይዘወተሩም አልፎ አልፎ ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ በምላስ ወለምታ፣ ባልሰማ ጆሮ፣ ወይም ባልሰከነ ሐሳብ ምክንያት መግባባት አለመቻል ከዚያም የመነጨ የተዛባ ግብረ መልስ መስጠት የሚያመጣው መዘዝ ሊኖር ይችላል፡፡

ሁልጊዜ አለመግባባት ራሱን በቻለ በሌላ አግባብ መታየት ሊኖርበት ይችላል፡፡ በአጋጣሚና አልፎ አልፎ በትዳር ውስጥ በምናስተላልፈው መልእክት ምክንያት የሚያጋጥሙ የግጭት ምክንያቶች ግን ስህተት ሲሆኑ የተሳሳተው ይቅርታን በመጠየቅ፣ የተበደለው ይቅርታ በማድረግ ግንኙነትን ወደነበረበት ሰላማዊ ሁኔታ መመለስ የባለትዳሮች ኃላፊነት ይሆናል፡፡ ይቅርታ የተሰበረ የግንኙነት ሁኔታን ለመቀጠል፣ ለመፈወስ እጅግ ከፍተኛ ሚና አለው፡፡

መሳሳትን ማጽናትም ሆነ መሳሳትን አለመፍቀድ ከጤናማ ግንኙነት ፈላጊዎች የሚጠበቅ አይሆንም፡፡ ሁሌ መሳሳትም ሆነ በአጋጣሚ የተፈጠሩ የግንኙነት ስህተቶችን በይቅርታ አለማየት የትዳር ግንኙነትን እጅግ ከፍተኛ አደጋ ላይ የሚጥሉ የፍቺ ዋዜማዎች ናቸው፡፡

ማጠቃለያ

መልካም ግንኙነት ባለበት ሁሉ መልካም ትዳር አለ፡፡ የመልካም ግንኙነት መሠረት ደግሞ መልካም ቃላት፣ መልካም ስነምግባር፣ አስተዋይነት፣ ዕውቀትና ይቅርባይነት ናቸው፡፡ እነዚህ ለትዳር ሕይወትን ይሰጡታል፡፡ ከታመመ ይፈውሱታል፡፡ ስለዚህም በመልካም ባለትዳሮች ልብ፣ ቃልና ሥራ ውስጥ ሁሉ አይለዩም፡፡

Health: ስኬታማ ትዳር እንዴት ይፈጠራል?

$
0
0

የዘመናችን አባባል ሆኖ ነው መሰልኝ «ባል ጠፋ፣ ሚስት የታል?» የሚሉ ሃሳቦች ሲሰነዘሩ እንሰማለን። እውነት ባልም ሚስትም ጠፍተው ነው? ሰው ትዳርን ሽሽት የጀመረው ወይስ ሌላ ምክንያት አለ ? ስል ሁሌ ራሴን እጠይቃለሁ። ምላሽ ባላገኝለትም። ለራሴ የማቀርበውን ጥያቄ የብዙዎች በመሆኑ ለምን የባለሙያ ምላሽ አይሰጥበትም በማለት ማፈላለግ ጀመርኩ። ተሳካልኝና የጋብቻና የቤተሰብ አማካሪውን አቶ ይመስገን ሞላን አገኘሁ። የእርሳቸውን አጠቃላይ ማብራሪያ ከማስቀደሜ በፊት በትዳር ውስጥ ያሉና ትዳርን በሩቁ የሚፈሩ ግለሰቦችን አስተያየት ለማስቀደም ወደድኩ።

marraige
መጀመሪያ ያናገርኩት ወጣት ዮሐንስ አለማየሁ ይባላል። የመጀመሪያ ድግሪ ምሩቅ ሲሆን፤ በአንድ የመንግሥት መስሪያ ቤት ተቀጣሪ ነው። ይህ ወጣት ወደ ትዳር ለመግባት የሚስት መጥፋት ብቻ አይደለም ማነቆው ይላል። በእርሱ ሃሳብ ትዳርን ለመጀመር ሦስት ነገሮች ያሰጉታል። አንደኛውና ዋንኛው እርሱ «ነፃነቴ» የሚለውን እንደ ልብ መውጣት መግባት፣ ያለ ሃሳብ ለራስ ብቻ መኖርን ወደ ትዳር ሲገባ እንደሚያጣው ማሰቡ ነው። ብቻውን በሚኖርበት ወቅት ከሚያደርጋቸው ነገሮች መታቀቡ ነፃነትን እንደመሸጥ ነው የሚቆጥረው። ሁለተኛው ደግሞ ለማግባት የሚያስባት ሴት ባህሪ «ቢቀየርብኝስ» የሚል ስጋት ስላሳደረበት ነው። ሦስተኛው ምክንያቱ የትዳር በር ላይ ቆሞ ሲመለከት ቤተሰብ የማስተዳደር አቅም ላይ ስጋት ይይዘዋል። ከአንድ ሁለት ከሁለትም ሦስት በሚሆንበት የትዳር ሂደት ውስጥ የተሻለ ገቢ የማይኖር ከሆነ «እንዴት ይገፋል?» የሚለው ዮሐንስ «ምን አለኝ» እያለ የብቸኝነት ኑሮውን በመግፋት ላይ መሆኑን ነው ያጫወተኝ።
ሌላዋ ወጣት ትንሳኤ ተስፋዝጊ «ባል ጠፋ» ከሚሉት ወገን ናት። ይቺ ወጣት ሴትነት ወደ ማዕድቤት በሆነበት የሃገራችን ወንዶች አመለካከት ለበለጠ ኃላፊነትና የሥራ ጫና መታጨት አልፈልግም የሚል አመለካከት አላት። በነፃነት እንደልቧ ወጥታ ከምትገባበት የቤተሰብ ኑሮ ወጥታ የራሷን ቤት መመሥረት ከባድ ኃላፊነት ሆኖ ነው የሚሰማት። «ትዳርን ሳስብ ይህን ኃላፊነት መሸከም እችላለሁ ብዬ ማሰብ ስለሚከብደኝ እፈራለሁ» የምትለው ትንሳኤ ከዚህም ሌላ ስጋት አላት።
«የሀገራችን ወንዶች መበለጥንና የሴት የበላይነትን መቀበል አይፈልጉም» ትላለች። እርሷ ደግሞ የማስትሬት ድግሪ ደረጃን የያዘች በመሆኗ የምትፈልገውን ዓይነት ባል ማግኘት ጭንቅ ሆኖባታል። «የተሻለ ደረጃ ላይ ያለው በጉራ እየተወጠረ የበታች የሆነው ደግሞ የራስ መተማመን መንፈስ እያጣ ባል የሚሆን ሰው ጠፍቶኛል።» ትላለች።
ትዳርን ሲያስቡት ከሚፈሩት ወጣቶች አስተያየት ከሰበሰብኩ በኋላ አዲስ ተጋቢዎችን ምን ገጠማችሁ? አልኳቸው። መጀመሪያው አካባቢ ለምን ሁሉም ሰው አያገባም የሚያሰኝ ጣፋጭና አስደሳች የፍቅር ጊዜ እንደነበረ የምትናገረው ወይዘሮ በእምነት ታዬ ናት። «ያ ጣፋጩ የፍቅር ጊዜ ተጠናቆ እውነተኛ ማንነት ሲገለጥ ከባዱ ፈተና ይጀምራል። አዲሷ ሙሽሪት ከሁሉ ነገር በላይ አሰልቺ የሆነባት የማያቋርጥና የእርሷን ኃላፊነት ብቻ የሚጠብቀው የቤት ወስጥ ሥራ ነው» በማለት ነው የምትገልጸው።
«ወላጆቼ ጋር እያለሁ እኔ ስፈልግ ብቻ ነበር በቤት ውስጥ ሥራ ተሳታፊ የምሆነው። በትዳር ውስጥ ያለውን የሥራ ጫና መቋቋም እቅቶኛል» የምትለው ወይዘሮ በእምነት በቤት ውስጥ ኃላፊነት በመጠመዷ ቀደም ሲል ለራሷ ብቻ የምትሰጠውን ጊዜ እንኳን ልታገኝ አለመቻሏን ትናገራልች፡፡
ሌላው የመጀመሪያ ችግር የሆነባት ተነጋግሮ መግባባት ያለመቻል ጉዳይ ነበር። «በፊት አንቺ እንዳልሽ ሲል የማውቀው የትዳር አጋሬ በእያንዳንዱ ነገር ተፅዕኖ ለማድረግና የእርሱን ንግግር ብቻ እንዳዳምጥ መፈለጉ ጭራሽ የማላውቀውን ሰው ነው እንዴ ያገባሁት? እንድል አድርጎኛል» ትላለች። ያምሆኖ ከተጋቡ 10 ወራትን ያስቆጠሩት እነ በእምነት ግንኙነታቸው ከዕለት ወደ ዕለት እየተሻሻለ መሄዱን አልደበቀችም። ትዳርም ቀድማ የፈራቻቸው የችግሮች ጥርቅም ሳይሆን በራሱ ከባድ ችግሮችን ተጋፍጦ የመቆየት ሂደት መሆኑን ነው የተማረችበት።
ትዳር የሁለት የተለያዩ ሰዎች ውህደት ውስጥ የሚፈጠር ጭንቀት ነው የሚለው ደግሞ አቶ ገመቺስ ጉደታ ነው። ዘወትር ግጭት፣ ጭቅጭቅ፣ ዝንት ዓለም ያለመግባባት ያለበት የሚመስለውን ትዳር በመተሳሰብ የተሻለ ማድረግ ይቻላል ባይ ነው።
አቶ ገመቺስ እያንዳንዱ በገንዘብ በኩል የሚመጡ ኃላፊነቶች ጫንቃው ላይ የወደቁ እስኪመስለው ድረስ በከባድ ውጥረት እራሱን ሲያስጨነቅ የቆየባቸውን ያለፉትን ጊዜዎች ሲያስብ ይቆጫል። «እንዲህ እንደአሁኑ በፕሮግራም መመራት እየተቻለ ምን ነበር ያስጨነቀኝ» ሲል ራሱን ታዝቧል።
በትዳር ውስጥ ያሉና ትዳርን በሩቁ የሚፈሩ ግለሰቦች የሰጡኝን አስተያየት ይዤ ወደ ሥነልቦና ባለሙያው አቶ ይመስገን ሞላ አመራሁ። የእርሳቸው ሙያዊ ማብራሪያ ለሁላችንም ምላሽ ይሰጣልና እንደሚከተለው አቀረብኩት።
ስኬታማ ትዳር የሚባለው ብለው ይጀምራሉ ባለሞያው «ስኬታም ትዳር የሚባለው ሁሉም እንዳለበት ቦታ ሲሆን ነው። ይህ ማለት ደግሞ ባልም እንደባል፣ ሚስትም እንደ ሚስት፣ ልጅም እንደ ልጅ ሲሆኑ ነው የቤተሰቡን ግንኙነት ጤናማ የሚያደርገው። የትዳር ሕይወትም መልካም ድምዳሜ ሲኖረው ስኬታማ ይባላል። ሁሉም መድረስ የሚገባው ላይ ሲደርስ ነው ስኬት ተብሎ የሚጠራው።
ከጋብቻ በፊት አንድ ግለሰብ በሁሉም አቅጣጫ እራሱን መሳደግ አለበት። ማለትም በገንዘብ በአዕምሮና በሌሎች መልኩ ማለት ነው። በየአቅጣጫው ራሱን የገነባ ሰው ሌላ ትክክለኛ ሰው ለማግኘት አይከብደውም። ይህ ከሆነ ደግሞ ከሁለት በትክክለኛ ሰዎች የተስተካከለ ትዳር ይመሠርታሉ። ለራሱ ክብር ያለውና ሙሉ ለሙሉ ትክክለኛ እንደሆነ የሚያምን ሰው ትክክለኛ ያልሆነ ሰው አያገባም እራሱንም በደንብ ስለሚያከብር ለማያከብረውና ዋጋውን ለሚያወርድበት ሰው ራሱን አሳልፎ አይሰጥም።
አንድ ሰው ማግባት ያለበት ዕድሜ ላይ ሲደርስ ለዕድሜው የሚመጥን አመለካከት ያለው ሰው ይሆናል ማለት ነው። ዋንኛው የትዳር መሠረት ባህሪ ሲሆን፤ ማንም ሰው ያለበትን መጥፎ ባህሪ ለማስተካከል ዓመታት አይወስድበትም። ጋብቻም ከመታሰቡ በፊት አለብኝ ብሎ የሚያምናቸውን ባህሪያት ማስወገድ የግድ ይላል።
የጋብቻ መጀመሪያ አካባቢ ሁለት የግል ሕይወትና የግል ማንንት ያላቸው ሰዎች እንጋባ ብለው ሲጀምሩ ከሁለት የተለያዩ ማንነቶች የመጡት ሁለቱ ሰዎች በተለይ እንደተጋቡ ሰሞን የጫጉላ ወቅት ትዳር ደስታ ብቻ ነው የሚሆነው።
በሁለተኛው ደረጃ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ነገሮች እንደተገመቱት አይሆንም። ይሆናል የተባለው ሁሉ ሳይሆንና የተገመተው ሲቀር ግጭቱ ከውስጥ ይጀምራል። እነዚህ ግጭቶች ግን ችግር ሳይሆኑ ሂደቶች ናቸው። ብዙ ሰዎች እነዚያን ሂደቶች በአግባቡ ማስሄድ ባለመቻላቸው ወደ ችግርነት ይቀየራሉ።
ሁለት የተለያዩ ሰዎች ሃያ ምናምን ዓመት በተለያየ ቤት፣ በተለያየ ኑሮ ፣በተለያየ ፍላጎት ፣ በተለያየ ባህል በተለያየ እውቀት አድገው አብረን እንኑር ሲሉ እንዲያውም የሚገርመው ባይጣሉ ነበር። መጣላታቸው ሁለቱም ራሳቸውን እየገለጹ ውስጣቸውን እያሳዩ ወደመተዋወቅ የሚያደርጉት ሂደት ነውና ይሚጠበቅ ነው።
ይህን ችግር ለመፍታት ግን እንዴት መግባባት እንደሚችሉ ማወቅ የግድ ነው። አንድ ሰው ምን እንደሚናገር ሳይሆን እንዴት እንደሚናገር ማወቅ አለበት። በየቀኑ በመጨቃጨቅ ወደቤት መግባት አስጠላኝ እስከሚባልበት ድረስ ማደግ የለበትም። ጭቅጭቅ የሚከሰተው አንድ ሰው የራሱን እምነት ማስረዳት ብቻ ስለሚፈልግ ነው። ይህ ሲሆን ደግሞ የትዳር አጋሬ ምን ሊል እየፈለገ ነው ብሎ ማዳመጥ እጀግ በጣም ተገቢ ነው። ለዚህም ነው መልስ ለመስጠት ከመቸኮል ይልቅ መደማመጥ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው የሚሆነው።
በጣም የሚገርመው በማይጠቅሙና በማይገቡ ነገሮች ሰዎች መጨቃጨቃቸው ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው ዕቃ ግዛ ተብሎ ረስቶቢገባ ለምን እንደረሳ መጠየቅና ማወቅ ተገቢ ነው። መርሳቱን ምክንያት አድርገው የሚፈጠሩ ምልልሶች ናቸው ጭቅጭቅ የሚሆኑት። የማይገቡና የማያስፈልጉ ባዶ ንዝንዞችን መተው የግድ ነው። ተግባቦት ማለት የሌላ ሰው ሃሳብና ሰሜትን መረዳት ነው፡፡ ያንን ለማድረግ አዳማጭ መሆን አስፈላጊ ነው። ስህተቶችን ለማረምና ለመረዳዳት ዕድል ይሰጣል።
ጋብቻ የጋራ ሕይወት ስለሆነ የየጋራ ኃላፊነትን ለመወጣት ማሰብ ችግሮችን የቀለለ እንዲሆን ያደርገዋል። ሁሉም ሰው የየራሱ ደርሻ አለው። የየራስ ኃላፊነቶችን በመወጣት ደረጃ ግንኙነት ሲደረግ መተጋገዝ ይሆናል። አንዱ የሌላውን ኃላፊነት ደርቦ መያዘ የነገን ግንኙነት አሰልቺ እንዲሆን ያደርገዋል። ይህ ደግሞ አደገኛ ነው።
ልጆች ከተወለዱ በኋላም ባልና ሚስቶች ራሳቸውን በብዙ ነገር ማዘጋጀት አለባቸው። ካልሆነ ግን የቤተሰቡ ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ የፍላጎትና የገቢ አለመመጣጠን ሲመጣ የሚያጋጩ ነገሮችም አብረው መፈጠራቸው አይቀርም። ለስኬታም ትዳር ባል እንደመሪ ሆኖ ሙሉ ለሙሉ የቤተሰብ ኃላፊነትን የሚወጣ ሲሆን፤ ሚስት እንደ ሽንፈት መቁጠር የለባትም። ሚስትም መሪዋን በማገዝ ሃሳብ በመካፈል መደገፍና ቤተሰቧን ማቆም ትችላለችና፡፡
ስኬታማ ትዳር ለመመሥረት መነጋገር፣ መደማመጥ፣ መከባበርና የሚከሰቱ ችግሮችን እንደ አመጣጣቸው መቀበል ያስፈልጋል። ይህን ለማድረግ የተዘጋጁ ተጋቢዎች የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ሁሉ በቀላሉ ለመፍታት አይቸገሩም። ውይይታቸው ወይም ንግግራቸው ወደ ጭቅጭቅ አያመራም። አንዳንድ ግለሰቦች ከውጪ ሆነው በሚፈጥሩት ጭንቀት ብቻ ትዳርን ጭራቅ አድርገው መሳላቸው ተገቢ አይሆንም። በመሆኑም በቅድሚያ በትዳር ለመጣመር ከማሰባቸው በፊት ራሳቸውን ለትዳር ዝግጁ ማድረግ ይገባቸዋል። ያኔ የተሳካ ትዳር ይሆንላቸዋል።

ጸሐፊ አስመረት ብስራት

Health: ስኬታማ ትዳር እንዴት ይፈጠራል?

$
0
0

የዘመናችን አባባል ሆኖ ነው መሰልኝ «ባል ጠፋ፣ ሚስት የታል?» የሚሉ ሃሳቦች ሲሰነዘሩ እንሰማለን። እውነት ባልም ሚስትም ጠፍተው ነውሰው ትዳርን ሽሽት የጀመረው ወይስ ሌላ ምክንያት አለ ስል ሁሌ ራሴን እጠይቃለሁ። ምላሽ ባላገኝለትም። ለራሴ የማቀርበውን ጥያቄ የብዙዎች በመሆኑ ለምን የባለሙያ ምላሽ አይሰጥበትም በማለት ማፈላለግ ጀመርኩ። ተሳካልኝና የጋብቻና የቤተሰብ አማካሪውን አቶ ይመስገን ሞላን አገኘሁ። የእርሳቸውን አጠቃላይ ማብራሪያ ከማስቀደሜ በፊት በትዳር ውስጥ ያሉና ትዳርን በሩቁ የሚፈሩ ግለሰቦችን አስተያየት ለማስቀደም ወደድኩ። 

መጀመሪያ ያናገርኩት ወጣት ዮሐንስ አለማየሁ ይባላል። የመጀመሪያ ድግሪ ምሩቅ ሲሆን፤ በአንድ የመንግሥት መስሪያ ቤት ተቀጣሪ ነው። ይህ ወጣት ወደ ትዳር ለመግባት የሚስት መጥፋት ብቻ አይደለም ማነቆው ይላል። በእርሱ ሃሳብ ትዳርን ለመጀመር ሦስት ነገሮች ያሰጉታል። አንደኛውና ዋንኛው እርሱ «ነፃነቴ» የሚለውን እንደ ልብ መውጣት መግባት፣ ያለ ሃሳብ ለራስ ብቻ መኖርን ወደ ትዳር ሲገባ እንደሚያጣው ማሰቡ ነው። ብቻውን በሚኖርበት ወቅት ከሚያደርጋቸው ነገሮች መታቀቡ ነፃነትን እንደመሸጥ ነው የሚቆጥረው። ሁለተኛው ደግሞ ለማግባት የሚያስባት ሴት ባህሪ «ቢቀየርብኝስ» የሚል ስጋት ስላሳደረበት ነው። ሦስተኛው ምክንያቱ የትዳር በር ላይ ቆሞ ሲመለከት ቤተሰብ የማስተዳደር አቅም ላይ ስጋት ይይዘዋል። ከአንድ ሁለት ከሁለትም ሦስት በሚሆንበት የትዳር ሂደት ውስጥ የተሻለ ገቢ የማይኖር ከሆነ «እንዴት ይገፋል?» የሚለው ዮሐንስ «ምን አለኝ» እያለ የብቸኝነት ኑሮውን በመግፋት ላይ መሆኑን ነው ያጫወተኝ። 

marraige

ሌላዋ ወጣት ትንሳኤ ተስፋዝጊ «ባል ጠፋ» ከሚሉት ወገን ናት። ይቺ ወጣት ሴትነት ወደ ማዕድቤት በሆነበት የሃገራችን ወንዶች አመለካከት ለበለጠ ኃላፊነትና የሥራ ጫና መታጨት አልፈልግም የሚል አመለካከት አላት። በነፃነት እንደልቧ ወጥታ ከምትገባበት የቤተሰብ ኑሮ ወጥታ የራሷን ቤት መመሥረት ከባድ ኃላፊነት ሆኖ ነው የሚሰማት። «ትዳርን ሳስብ ይህን ኃላፊነት መሸከም እችላለሁ ብዬ ማሰብ ስለሚከብደኝ እፈራለሁ» የምትለው ትንሳኤ ከዚህም ሌላ ስጋት አላት።

«የሀገራችን ወንዶች መበለጥንና የሴት የበላይነትን መቀበል አይፈልጉም» ትላለች። እርሷ ደግሞ የማስትሬት ድግሪ ደረጃን የያዘች በመሆኗ የምትፈልገውን ዓይነት ባል ማግኘት ጭንቅ ሆኖባታል። «የተሻለ ደረጃ ላይ ያለው በጉራ እየተወጠረ የበታች የሆነው ደግሞ የራስ መተማመን መንፈስ እያጣ ባል የሚሆን ሰው ጠፍቶኛል።» ትላለች። 

ትዳርን ሲያስቡት ከሚፈሩት ወጣቶች አስተያየት ከሰበሰብኩ በኋላ አዲስ ተጋቢዎችን ምን ገጠማችሁአልኳቸው። መጀመሪያው አካባቢ ለምን ሁሉም ሰው አያገባም የሚያሰኝ ጣፋጭና አስደሳች የፍቅር ጊዜ እንደነበረ የምትናገረው ወይዘሮ በእምነት ታዬ ናት። «ያ ጣፋጩ የፍቅር ጊዜ ተጠናቆ እውነተኛ ማንነት ሲገለጥ ከባዱ ፈተና ይጀምራል። አዲሷ ሙሽሪት ከሁሉ ነገር በላይ አሰልቺ የሆነባት የማያቋርጥና የእርሷን ኃላፊነት ብቻ የሚጠብቀው የቤት ወስጥ ሥራ ነው» በማለት ነው የምትገልጸው።

«ወላጆቼ ጋር እያለሁ እኔ ስፈልግ ብቻ ነበር በቤት ውስጥ ሥራ ተሳታፊ የምሆነው። በትዳር ውስጥ ያለውን የሥራ ጫና መቋቋም እቅቶኛል» የምትለው ወይዘሮ በእምነት በቤት ውስጥ ኃላፊነት በመጠመዷ ቀደም ሲል ለራሷ ብቻ የምትሰጠውን ጊዜ እንኳን ልታገኝ አለመቻሏን ትናገራልች፡፡

ሌላው የመጀመሪያ ችግር የሆነባት ተነጋግሮ መግባባት ያለመቻል ጉዳይ ነበር። «በፊት አንቺ እንዳልሽ ሲል የማውቀው የትዳር አጋሬ በእያንዳንዱ ነገር ተፅዕኖ ለማድረግና የእርሱን ንግግር ብቻ እንዳዳምጥ መፈለጉ ጭራሽ የማላውቀውን ሰው ነው እንዴ ያገባሁትእንድል አድርጎኛል» ትላለች። ያምሆኖ ከተጋቡ 10 ወራትን ያስቆጠሩት እነ በእምነት ግንኙነታቸው ከዕለት ወደ ዕለት እየተሻሻለ መሄዱን አልደበቀችም። ትዳርም ቀድማ የፈራቻቸው የችግሮች ጥርቅም ሳይሆን በራሱ ከባድ ችግሮችን ተጋፍጦ የመቆየት ሂደት መሆኑን ነው የተማረችበት።

ትዳር የሁለት የተለያዩ ሰዎች ውህደት ውስጥ የሚፈጠር ጭንቀት ነው የሚለው ደግሞ አቶ ገመቺስ ጉደታ ነው። ዘወትር ግጭት፣ ጭቅጭቅ፣ ዝንት ዓለም ያለመግባባት ያለበት የሚመስለውን ትዳር በመተሳሰብ የተሻለ ማድረግ ይቻላል ባይ ነው።

አቶ ገመቺስ እያንዳንዱ በገንዘብ በኩል የሚመጡ ኃላፊነቶች ጫንቃው ላይ የወደቁ እስኪመስለው ድረስ በከባድ ውጥረት እራሱን ሲያስጨነቅ የቆየባቸውን ያለፉትን ጊዜዎች ሲያስብ ይቆጫል። «እንዲህ እንደአሁኑ በፕሮግራም መመራት እየተቻለ ምን ነበር ያስጨነቀኝ» ሲል ራሱን ታዝቧል።

በትዳር ውስጥ ያሉና ትዳርን በሩቁ የሚፈሩ ግለሰቦች የሰጡኝን አስተያየት ይዤ ወደ ሥነልቦና ባለሙያው አቶ ይመስገን ሞላ አመራሁ። የእርሳቸው ሙያዊ ማብራሪያ ለሁላችንም ምላሽ ይሰጣልና እንደሚከተለው አቀረብኩት።

ስኬታማ ትዳር የሚባለው ብለው ይጀምራሉ ባለሞያው «ስኬታም ትዳር የሚባለው ሁሉም እንዳለበት ቦታ ሲሆን ነው። ይህ ማለት ደግሞ ባልም እንደባል፣ ሚስትም እንደ ሚስት፣ ልጅም እንደ ልጅ ሲሆኑ ነው የቤተሰቡን ግንኙነት ጤናማ የሚያደርገው። የትዳር ሕይወትም መልካም ድምዳሜ ሲኖረው ስኬታማ ይባላል። ሁሉም መድረስ የሚገባው ላይ ሲደርስ ነው ስኬት ተብሎ የሚጠራው። 

ከጋብቻ በፊት አንድ ግለሰብ በሁሉም አቅጣጫ እራሱን መሳደግ አለበት። ማለትም በገንዘብ በአዕምሮና በሌሎች መልኩ ማለት ነው። በየአቅጣጫው ራሱን የገነባ ሰው ሌላ ትክክለኛ ሰው ለማግኘት አይከብደውም። ይህ ከሆነ ደግሞ ከሁለት በትክክለኛ ሰዎች የተስተካከለ ትዳር ይመሠርታሉ። ለራሱ ክብር ያለውና ሙሉ ለሙሉ ትክክለኛ እንደሆነ የሚያምን ሰው ትክክለኛ ያልሆነ ሰው አያገባም እራሱንም በደንብ ስለሚያከብር ለማያከብረውና ዋጋውን ለሚያወርድበት ሰው ራሱን አሳልፎ አይሰጥም።

አንድ ሰው ማግባት ያለበት ዕድሜ ላይ ሲደርስ ለዕድሜው የሚመጥን አመለካከት ያለው ሰው ይሆናል ማለት ነው። ዋንኛው የትዳር መሠረት ባህሪ ሲሆን፤ ማንም ሰው ያለበትን መጥፎ ባህሪ ለማስተካከል ዓመታት አይወስድበትም። ጋብቻም ከመታሰቡ በፊት አለብኝ ብሎ የሚያምናቸውን ባህሪያት ማስወገድ የግድ ይላል።

የጋብቻ መጀመሪያ አካባቢ ሁለት የግል ሕይወትና የግል ማንንት ያላቸው ሰዎች እንጋባ ብለው ሲጀምሩ ከሁለት የተለያዩ ማንነቶች የመጡት ሁለቱ ሰዎች በተለይ እንደተጋቡ ሰሞን የጫጉላ ወቅት ትዳር ደስታ ብቻ ነው የሚሆነው። 

በሁለተኛው ደረጃ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ነገሮች እንደተገመቱት አይሆንም። ይሆናል የተባለው ሁሉ ሳይሆንና የተገመተው ሲቀር ግጭቱ ከውስጥ ይጀምራል። እነዚህ ግጭቶች ግን ችግር ሳይሆኑ ሂደቶች ናቸው። ብዙ ሰዎች እነዚያን ሂደቶች በአግባቡ ማስሄድ ባለመቻላቸው ወደ ችግርነት ይቀየራሉ። 

ሁለት የተለያዩ ሰዎች ሃያ ምናምን ዓመት በተለያየ ቤት፣ በተለያየ ኑሮ ፣በተለያየ ፍላጎት ፣ በተለያየ ባህል በተለያየ እውቀት አድገው አብረን እንኑር ሲሉ እንዲያውም የሚገርመው ባይጣሉ ነበር። መጣላታቸው ሁለቱም ራሳቸውን እየገለጹ ውስጣቸውን እያሳዩ ወደመተዋወቅ የሚያደርጉት ሂደት ነውና ይሚጠበቅ ነው።

ይህን ችግር ለመፍታት ግን እንዴት መግባባት እንደሚችሉ ማወቅ የግድ ነው። አንድ ሰው ምን እንደሚናገር ሳይሆን እንዴት እንደሚናገር ማወቅ አለበት። በየቀኑ በመጨቃጨቅ ወደቤት መግባት አስጠላኝ እስከሚባልበት ድረስ ማደግ የለበትም። ጭቅጭቅ የሚከሰተው አንድ ሰው የራሱን እምነት ማስረዳት ብቻ ስለሚፈልግ ነው። ይህ ሲሆን ደግሞ የትዳር አጋሬ ምን ሊል እየፈለገ ነው ብሎ ማዳመጥ እጀግ በጣም ተገቢ ነው። ለዚህም ነው መልስ ለመስጠት ከመቸኮል ይልቅ መደማመጥ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው የሚሆነው።

በጣም የሚገርመው በማይጠቅሙና በማይገቡ ነገሮች ሰዎች መጨቃጨቃቸው ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው ዕቃ ግዛ ተብሎ ረስቶቢገባ ለምን እንደረሳ መጠየቅና ማወቅ ተገቢ ነው። መርሳቱን ምክንያት አድርገው የሚፈጠሩ ምልልሶች ናቸው ጭቅጭቅ የሚሆኑት። የማይገቡና የማያስፈልጉ ባዶ ንዝንዞችን መተው የግድ ነው። ተግባቦት ማለት የሌላ ሰው ሃሳብና ሰሜትን መረዳት ነው፡፡ ያንን ለማድረግ አዳማጭ መሆን አስፈላጊ ነው። ስህተቶችን ለማረምና ለመረዳዳት ዕድል ይሰጣል።

ጋብቻ የጋራ ሕይወት ስለሆነ የየጋራ ኃላፊነትን ለመወጣት ማሰብ ችግሮችን የቀለለ እንዲሆን ያደርገዋል። ሁሉም ሰው የየራሱ ደርሻ አለው። የየራስ ኃላፊነቶችን በመወጣት ደረጃ ግንኙነት ሲደረግ መተጋገዝ ይሆናል። አንዱ የሌላውን ኃላፊነት ደርቦ መያዘ የነገን ግንኙነት አሰልቺ እንዲሆን ያደርገዋል። ይህ ደግሞ አደገኛ ነው። 

ልጆች ከተወለዱ በኋላም ባልና ሚስቶች ራሳቸውን በብዙ ነገር ማዘጋጀት አለባቸው። ካልሆነ ግን የቤተሰቡ ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ የፍላጎትና የገቢ አለመመጣጠን ሲመጣ የሚያጋጩ ነገሮችም አብረው መፈጠራቸው አይቀርም። ለስኬታም ትዳር ባል እንደመሪ ሆኖ ሙሉ ለሙሉ የቤተሰብ ኃላፊነትን የሚወጣ ሲሆን፤ ሚስት እንደ ሽንፈት መቁጠር የለባትም። ሚስትም መሪዋን በማገዝ ሃሳብ በመካፈል መደገፍና ቤተሰቧን ማቆም ትችላለችና፡፡ 

ስኬታማ ትዳር ለመመሥረት መነጋገር፣ መደማመጥ፣ መከባበርና የሚከሰቱ ችግሮችን እንደ አመጣጣቸው መቀበል ያስፈልጋል። ይህን ለማድረግ የተዘጋጁ ተጋቢዎች የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ሁሉ በቀላሉ ለመፍታት አይቸገሩም። ውይይታቸው ወይም ንግግራቸው ወደ ጭቅጭቅ አያመራም። አንዳንድ ግለሰቦች ከውጪ ሆነው በሚፈጥሩት ጭንቀት ብቻ ትዳርን ጭራቅ አድርገው መሳላቸው ተገቢ አይሆንም። በመሆኑም በቅድሚያ በትዳር ለመጣመር ከማሰባቸው በፊት ራሳቸውን ለትዳር ዝግጁ ማድረግ ይገባቸዋል። ያኔ የተሳካ ትዳር ይሆንላቸዋል።

ጸሐፊ አስመረት ብስራት 

Health: የፀጉር መበጣጠስን ለማስቀረት 5 ቀላል ዘዴዎች

$
0
0

Young woman holding hair against white background

የፀጉር መበጣጠስን ለማስቀረት በሚል ውድ የውበት መጠበቂያና የፀጉር መንከባከቢያ ውጤቶችን ከመሸመት ይልቅ በቀላሉ የምናገኛቸውን ነገሮች እና ተፈጥሯዊ ዘዴዎችን በመጠቀም ለፀጉራችን እንክብካቤ ማድረጉ የሚመረጥ ሲሆን፥ የውበት ባለሙያዎችም ይህንኑ እንድናደርግ ነው የሚመክሩን።

በመሆኑም እነዚህን አምስት አማራጮች እንድንተገብራቸው ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ያወጣው መረጃ ይመክራል።

1.ዘይት መጠቀም፣

የወይራ ዘይት፣ የኮኮናት ዘይት አልያም ሌላ ማንኛውንም አይነት ዘይት ወስደን እናፈላዋለን፤ ከዚያም ለብ ሲል በጥንቃቄ የፀጉራችንን ስር በደንብ እያዳረስን እንቀባዋለን፤ ለአንድ ሰዓት ያህልም በሻሽ ወይም ፎጣ ጠቅልለን ካቆየን በኋላ በሻምፖ እንለቃለቀዋለን።

2. ተፈጥሯዊ ጭማቂዎች (ጂውሶችን) መጠቀም፣

አመሻሽ ላይ የነጭ፣ ቀይ ሽንኩርት አልያም የዝንጅብል ጭማቂን ወስደን በተመሳሳይ የፀጉራችን ስሩን በደንብ መቀባት፤ ከዚያም በማግስቱ ልንለቃለቀው እንችላለን።

3. የጭንቅላት ማሳጅ (መታሸት)

የፀጉራችን ስር አካባቢ ለተወሰኑ ደቂቃዎች በየቀኑ የምናደርገው የማሸት (ማሳጅ) የማድረግ ተግባር የደም ዝውውርን የሚያቀላጥፍ ሲሆን፥ የደም ዝውውር መቀላጠፍም በአንፃሩ የፀጉር ሴሎችን እድገት ያነቃቃል።

4.አረንጓዴ ሻይ መጠቀም፣

ሁለት የአረንጓዴ ሻይ ከረጢት በአንድ ኩባያ የፈላ ውሃ ላይ በመጠቀም የፀጉራችንን የስረኛው ክፍል መቀባት፣ ለአንድ ሰዓት ያህል ካቆየነው በኋላም እንደምንፈልገው ልንለቃለቀው እንችላለን።

በአረንጓዴ ሻይ ውስጥ የምናገኘው አንቲኦክሲዳንትስ የፀጉር መነቃቀልን ይከላከላል።

በተጨማሪም የፀጉር ዕድገትን ያፋጥናል።

5. ጭንቀትን ማስወገድ፣

ለፀጉር መሳሳት እና መነቃቀል አብይ ምክንያት ተደርጎ የሚወሰደው ጭንቀት ነው።

በመሆኑም ከአላስፈላጊ ጭንቀት ራስን መከላከል እና የተመስጦ (ሜዲቴሽን) ተግባርን በማከናወን የፀጉር መነቃቀልንም ሆነ መሳሳትን መከላከል ይቻላል።

ተመስጦ በተጨማሪም የሆርሞን መመጣጠን እንዲኖር በማገዝ የፀጉር እድገት ፍጥነትን እንደሚጨምርም ነው የሚነገረው።

ምንጭ፦ timesofindia.indiatimes.com

Health: ሁልጊዜ የድካም ስሜት እንዲሰማዎ የሚያደረጉ 7 ምክንያቶች

$
0
0

always tiredReason’s you’re always tired

(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም)

1• አካል ብቃት እንቅስቃሴ አያደርጉም
2• በቂ ውሃን አይጠጡም
3• አይረን የሚባል ንጥረ ነገር ያላቸውን ምግቦች አያዘወትሩም
4• ቁርስዎን አይመገቡም
5• ለጤና ተስማሚ ከሆኑ ምግቦች ይልቅ ጣፋጭ እና ቅባታማ ምግቦችን ይመገባሉ
6• የሥራ ቦታዎ የተዘበራረቀ እና ያልተስተካከለ ከሆነ ነው
7 • በሥራ ምክንያት ሰለሚያመሹ በቂ እንቅልፍ አለማግኝትዎ ነው፡፡
ጤና ይስጥልኝ

• You don’t have enough exercise
• You don’t drink enough water
• You’re not consuming enough iron
• Skipping your breakfast
• Eating too much junk food
• You have a messy office
• You always stay up late

Health: የእከክ ህመም ምልክቶች –ሕክምናውና ሊደረግ የሚገባው ጥንቃቄ

$
0
0

እከክ ቆዳን የሚያሳክክ በቆዳ ስር በሚቀመጡ ሳርኮፕቴስ እስኬቢስ በሚባሉ ተዋሲያን የሚከሰት የቆዳ ላይ ችግር ነዉ፡፡ ህመሙ በቤተሰብ፣ በህፃናት እንክብካቤ ማዕከል፣ ትምህርት ቤቶች፣የህመሙማን መንከባከቢያ ማዕከልና እስር ቤቶች ዉስጥ በቀላሉ በአካላዊ ንክኪ ሊተላለፍ የሚችል የህመም አይነት ነዉ፡፡
itchy skin
በቆዳዎ ላይ ሊቀቡ የሚችሉ ምድሃኒቶች በሽታዉን ሊያመጡ የሚችሉ ተዋሲያንንና እንቁላላቸዉን በቀላሉ የሚገድል ነዉ፡፡

የህመሙ ምልክቶች፡-

· የቆዳ ማሳከክ፡- ብዙዉን ጊዜ ከፍ ያለና ማታ ማታ የሚባባስ
· ቀጫጭን የሆኑ የተቦረቦሩ የቆዳ ላይ ቁስለቶች መታየት

የተቦረቦሩ ቁስለቶች በተጣጠፉ የቆዳ ክፍሎች ላይ በብዛት ይታያል፡፡ እከክ ምንም እንኳ በየትኛዉም የሰዉነት ቆዳ ላይ ቢከሰትም በተለይ በሚከተሉት የሰዉነት ክፍሎች አካባቢ በብዛት ይከሰታል፡-
· በጣቶች መካከል
· በብብት ስር
· በወገብ አካባቢ
· በዉስጠኛዉ የእጅዎ ክፍል
· በዉስጠኛዉ የክርን ክፍል
· በዉስጥ እግር
· ጡት አካባቢ
· በወንዶች ብልት አካባቢ
· በመቀመጫ አካባቢ
· በጉልበት አካባቢ ናቸዉ፡፡

ከዚህ በፊት በእከክ ተይዘዉ ከነበረ አሁን በድጋሚ ቢያዙ የህመሙ ምልክቶች በጥቂት ቀናት ዉስጥ የሚታይ ሲሆን ከዚህ በፊት በእከክ ተይዘዉ የማያዉቁ ከሆነ ግን የህመሙ ምልክቶች ለመታየት እስከ 6 ሳምንታት ሊወስድ ይችላል፡፡ ማስታወስ የሚገባዎ ነገር ቢኖር ምንም እንኳ የህመሙ ምልክት ባይታይቦትም በሽታዉን ሊያሰራጩ እንደሚችሉ ነዉ፡፡ ቅርበት ያለዉ አካላዊ ግንኙነትና ልብስን ወይም መኝታን መጋራት ለህመሙ መዛመት/መተላለፍ ዋነኛዉ መንገድ ነዉ፡፡

ሊደረግ የሚችል ህክምና

የእከክ ህክምና የበሽታዉን አምጭ ተዋሲያን ማጥፋት ሲሆን በክሬምና በሎሽን መልክ ያሉ መድሃኒቶች ሊታዘዙ ይችላሉ፡፡እከክ በቀላሉ የሚተላለፍ የቆዳ ላይ ችግር ስለሆነ ሌሎች የቤተሰብ አባላት የህመሙ ምልክቶች ባይኖራቸዉም የህክምና ባለሙያዎ መድሃኒቱን ለሁሉም የቤተሰብ አባላትዎ ሊያዝ ይችላል፡፡

እንዴት መከላከል ይቻላል?

ህመሙ ተመልሶ እንዳይዞትና ወደ ሌሎች ሰዎች እንዳይተላለፍ ሁሉንም ልብሶችዎንና አንሶላዎችን በንፅህና ማፅዳት፡፡ ይህም በሞቀ ዉሃና ሳሙና ልብሶችን፣ ፎጣዎችንና አንሶላዎችን ህክምና ከመጀመርዎ ከሶስት ቀናት በፊት የተጠቀሙባቸዉን በሙል በደንብ ካጠቡ በኃላ በሙቀት ማድረቅ፡፡ በዉሃ መታጠብ የማይችሉትን ደግሞ በፀሃይ ብርሃን ማድረቅ/ማሞቅ ናቸዉ፡፡

Health: ቋቁቻ የቆዳ ችግር እንዴት ይድናል?

$
0
0

quqqucha

ቋቁቻ  በብዛት ሊከሰት የሚችል ከሰዉ ወደ ሰዉ የማይተላለፍ በፈንገስ ምክንት የሚመጣ የቆዳ ላይ ችግር ነዉ::
ፈንገሱ የቆዳ ተፈጥሮዊ መልክን በማሳጣት ትናንሽ፣ነጣ ወይም ጠቆር ያሉ መልካቸዉን የለወጡ ነገሮች በቆዳ ላይ እንዲወጡ ያደርጋል፡፡ ቐቁቻ በብዛት የሚከሰትዉ በአንገት፣ትከሻ ደረትና ጀርባ ላይ ነዉ፡፡

የህመሙ ምልክቶች

· በጀረባ፣ ደረት፣ አንገት፣ እጅ ላይ (ከክርን በላይ ከፍ ብሎ ባለዉ) የቆዳ ከለር መለወጥ

· መጠነኛ ማሳከክ
· የቆዳ መቀረፍ የመሳሰሉት ናቸዉ፡፡

የህመሙ መንስኔዎች

ቋቁቻን ሊያመጡ የሚችሉ ፈንገሶች በጤናማ ቆዳ ላይ ሊገኙ ይችላሉ፡፡ ይህ ችግር በብዛት በለጋነትና በወጣትነት እድሜ ክልል ይከሰታል፡፡ ቐቁቻ ህመም የለዉም፤ ከሰዉ ወደ ሰዉ አይተላለፍም፡፡ ነገር ግን ሊያስጨንቅ ወይም የሀፍረት ስሜት እንዲሰማን ሊያደርግ ይችላል፡፡ ይህ የሚሆነም ፈንገሱ ከመጠን በላይ ሲያድግ ነዉ፡፡ ቐቁቻ እንዲመጣ የሚያደርጉ/እንዲባባስ የሚያደርጉ ነገሮች:-
· ሞቃታማና እችጥበታማ የአየር ፀባይ
· ወዛማ ቆዳ ካለዎት
· የሆርሞን መለዋወጥ
· የበሽታ መከላከል መዳከም ናቸዉ፡፡

የህክምና ባለሙያዎን መመከር የሚገባዎ መቼ

· ለቆዳዎ እያደረጉት ያለዉ ጥንቃቄ ለዉጥ ካላመጣ
· ህመሙ ከጠፋ በኃላ ተመልሶ ከመጣ
· ህመሙ ብዙ የቆዳ ክፍልን ከሸፈነ

ሊደረጉ የሚችሉ ህክምናዎች
ቋቁቻ በፈንገስ ምክንት የሚመጣ የቆዳ ችግር ስለሆነ የሚከተሉት መድሃኒቶች ሊታዘዙ ይችላሉ፡፡ የተወሰኑት መድሃኒቶች በቆዳ ላይ ሊቀቡ የሚችሉ ሲሆን ቀሪዎቹ የሚዋጡ ናቸዉ፡፡
· የፍሉኮናዞል እንክብል ወይም ፈሳሽ መድሃኒት
· ኢትራኮናዞል( እንክብል፣ካፕሲዩል ወይም ፈሳሽ)
· ኬቶኮናዞል( ክሬም፣ ጄል ወይም ሻንፖ) ናቸዉ፡፡

ምንም እንኳ ህክምናዉን በደንብ ቢከታተሉትና ህመሙ ቢሻሎትም ለሳምንታት ወይም ለወራት የቆዳዎ ቀለምዎ ሳይለወጥና እንደሻከረ ሊቀጥል ይችላል፡፡ እነዳንዴ ደግሞ ህመሙ ተመልሶ ሊመጣ ይችላል( በተለይ በሞቃታማና እርጥበታማ የአየር ፀባይ ወቅት)፡፡ ስለሆነም ኢንፌክሽኑ ተመልሶ እንዳይመጣ መድሃኒት በወር አንዴ ወይም ሁለቴ መዉሰድ ሊስፈልግ ይችላል፡፡


Health: የጥቁር አዝሙድ የጤና ጥቅሞች

$
0
0

(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)
*ለካንሰር ህመም
የክሮሽያ ተመራማሪዮች ጥቁር አዝሙድ በውስጡ የያዛቸው ንጥረ ነገሮች የካንሰር ሴሎችን የመቀነስ ሀይል እንዳለው ይናገራሉ።
*ለጤናማ ጉበት
ጥቁር እዝሙድ ለጉበት ጤና እጅግ ጠቃሚ ሲሆን መድሀኒት በብዛት በመውሰድ፣ በአልኮል መጠጥ ወይንም በሌሎች ህመሞች ምክንያት የተጎዳን ጉበት የመዳን ሂደትን ያፋጥናል።
*ለቆዳ ጤናማነት
ቆዳችንን ከጉዳት የመከላከል ጥቅምን ይሰጣል
*ለጤናማ ፀጉር
ጥቁር አዝሙድ ለፀጉር ተስማሚ የሆኑ ንጥረ ነገሮችን ስለያዘ የፀጉር መነቃቀል እንዳይኖር ይረዳል። ከዚህም በተጨማሪ ጠንካራ እንዲሆን ያደርጋል።
tikur azmud

Black Seed Oil Benefits

Of the many ways that black seed oil benefits the body, the 6 that stick out in the scientific literature its ability to help prevent cancer, diabetes, obesity, hair loss, skin disorders and infections like MRSA.

Cancer

Croatian scientists evaluated the antitumor activity of thymoquinone and thymohydroquinone in mice and discovered that the two phytochemicals in black seed oil can resulted in 52% decrease in tumor cells!

Being rich in both chemicals, black seed is unique in that it can help prevent and treat cancer through a variety of mechanisms:

Anti-proliferation
Apoptosis induction
Cell cycle arrest
Reactive oxygen species generation
Anti-metastasis
Anti-angiogenesis
According to one study,

“The anti-tumor effects of thymoquinone have also been investigated in tumor xenograft mice models for colon, prostate, pancreatic and lung cancer. The combination of thymoquinone and conventional chemotherapeutic drugs could produce greater therapeutic effect as well as reduce the toxicity of the latter.”

Liver Health

The liver is one of the most important organs in the body. Nearly every toxin gets processed through the liver, and the bile from the liver is the key to digesting fats and keeping your mind and body happy and healthy. For those that have struggled with poor liver function due to medication side effects, alcohol consumption, or disease, black seed oil could greatly speed the healing process. In a recent study scientists discovered that black seed oil benefits the function of the liver and helps prevent both damage and disease.

Diabetes

Explained in a recent article published by the Journal of Endocrinology and Metabolism, researchers from the Indian Council of Medical Research highlight that black seed oil “causes gradual partial regeneration of pancreatic beta-cells, increases the lowered serum insulin concentrations and decreases the elevated serum glucose.” This is actually quite profound because Nigella sativa is one of the few substances on the planet that is suggested to help prevent both type 1 and type 2 diabetes.

In fact, according to the study, black seed “improves glucose tolerance as efficiently as metformin; yet it has not shown significant adverse effects and has very low toxicity!” This is HUGE because metformin, one of the most commonly prescribed type 2 diabetes drugs, can cause a wide slew of side effects including:

Bloating
Constipation/Diarrhea
Flushing of the skin
Gas/Indigestion
Heartburn
Headache
Nail changes
Metallic taste in mouth
Muscle pain
Stomach pain
Weight Loss

The Journal of Diabetes and Metabolic Disorders published a study last June systemically reviewing the literature for plants that have anti-obesity properties and discovered that black seed oil was amongst the most effective natural remedies on the planet.

Not traditionally believed to treat obesity, Nigella sativa is a marvelous anti-inflammatory agent that is known to help people lose weight in the same way that it helps diabetics. Specifically, by decreasing these weight gain triggers, black seed oil has helped millions shed excess weight:

Appetite
Glucose absorption in the intestine
Liver gluconeogenesis
Blood glucose levels
Cholesterol
Triglycerides
Healthy Hair

Probably one of the most unique black seed oil benefits is its uncanny ability to help restore hair loss. No one quite understands why it happens, but it’s not too hard to guess that it has something to do with its powerful antioxidant and antimicrobial properties. By strengthening hair follicles, there is very good reason to see how black seed oil can help promote strengthened hair roots.

Healthy Skin

Produced in the retina, choroid and epidermis, melanin are pigments that protect the skin from damage. You probably are most family with it being the main chemical responsible for giving our eyes and skin their individual color. Known to promote and inhibit melanogenesis (melanin production), black seed oil benefits on the skin and other cells are profoundly healing.

For example, in a recent study conducted by Iranian researchers, Nigella saliva was found as effective as the skin cream Betamethasone in improving quality of life and decreasing severity of hand eczema. When you consider that black seed oil has virtually no side effects, the benefits of Nigella, in fact, far exceed medical intervention!

Infections (MRSA)

Of all the superbugs that black seed oil can kill, Methicillin resistant Staphylococcus aureus (MRSA) is one of the most important. MRSA is plaguing hospitals and nursing homes across the globe because ordinary staph infections are becoming resistant to generic antibiotics. The elderly population is especially at risk because it is generally associated with invasive procedures such as surgeries, intravenous tubing, and artificial joints. Primarily due to weakened immunity, the growing population of senior citizens has made MRSA a global public health risk.

Thankfully, one of the strongest black seed oil benefits comes to the rescue. Pakistan scientists took several strains of MRSA and discovered that each one was sensitive to N. Sativa, proving that black seed oil can help slow down or stop MRSA from spreading out of control.

Health: የጨጓራ ሕመም

$
0
0

Gastric Ulcer
(በዶክተር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)

► የጨጓራ ሕመም የሚከሰተው በጨጓራችን ግድግዳ ላይ ቁስለት በሚያስከትሉ ምክንያቶችነው፡፡

እነዚህም፡-
✔ ለጨጓራ ተስማሚ ያልሆኑ መድሃኒቶችን በመውሰድ
✔ የባክቴሪያ ኢንፌክሽን
✔ ከፍተኛ የአልኮል መጠጥ መውሰድ
✔ ቅመም የበዛባቸው ምግቦች መመገብ
✔ ጭንቀት
✔ ሲጋራ ማጤስ
✔ መርዛማ ኬሚካሎች ወደ ሆድ ማስገባት

► የጨጓራ ሕመም ምልክቶች ምንድን ናቸው?

የጨጓራ ሕመም ምልክቶች ከሰውስው የሚለያዩ ቢሆንም በአብዛኛው ግን እነዚህን ያካትታሉ፡፡

✔ የማቅለሽለሽ ስሜት
✔ የሆድ መንፋት ስሜት
✔ ማስመለስ
✔ የምግብ አለመፈጨት
✔ የማቃጠል ስሜት በተለይ ከምግብ በኋላ
✔ የምግብ ፍላጎት መቀነስ
✔ የሠገራ ቀለም መለወጥ ወይም መጥቆር ናቸው

ከባድ የሆነ የጨጓራ ሕመም ያላቸው ሰዎች የጨጓራ ቁስለት እና መድማት ሊከሰትባቸው ስለሚችል በተጨማሪ እነዚህ ምልክቶች ሊታይባቸው ይችላሉ፡፡

✔ የማላብ ስሜት
✔ የልብ ምት መጨመር
✔ የትንፋሽ ማጠር
✔ ከፍተኛ የሆነ የማቃጠል ስሜት
✔ ደም ማስመለስ
✔ ደም የቀላቀለና ከወትሮው የተለየ መጥፎ ሽታ ያለው ሠገራ መኖር ናቸው፡፡

እነዚህ ዓይነት ምልክቶች ያሉበት ሰው ወደ ሕክምና ማዕከል በመሄድ ተገቢ የሆነውን ምርመራና ሕክምና ማግኘት ይኖርበታል፡፡

የሕክምናው ሁኔታ የጨጓራ ሕመሙ እንደተከሰተበት ምክንያት ሊለያይ ቢችልም ያሉትን ምልክቶች በማስወገድ ለሕመምተኛው ፋታ መስጠትና ሕምሙን ያስከተላውን ሁኔታ በምርመራዎች አረጋግጦ መፍትሔ መስጠት ተገቢ ነው፡፡

የጨጓራ ሕመምን ሊያስነሱብን የሚችሉ ማናቸውንም ነገሮች በማስወገድ ሕምሙ እንዳይቀሰቀስብን ማድረግ ይቻላል፡፡

ጤና ይስጥልኝ

የስንፈተ ወሲብ –ከ10 በላይ ምክንያቶችና ከ10 በላይ መፍትሄዎች!!

$
0
0

 

ይህ ጽሁፍ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ላይ ታትሞ ወጥቷል::

በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት የሚፈጠር ችግርን በግልፅ ተነጋግሮ፣ መፍታትን ባህሉ ባደረገ ማህበረሰብ ውስጥ የስንፈተ ወሲብ ችግር የትዳር አደጋ የመሆኑ ጉዳይ ብዙም አሳሳቢ ላይሆን ይችላል፡፡

ሀገራችንን ጨምሮ በአፍሪካና በኤዢያ በትዳር ተጣማሪዎች መካከል በግልፅ የመነጋገር ባህል የዳበረ እንዳልሆነ በስነ ማህበረሰብ ሙያተኞች የተጠኑ ጥናቶች ያረጋግጣሉ፡፡ ስንፈተ ወሲብ ፆታና ዕድሜ ሳይለይ ይከሰታል፡፡ አደጋ የሚሆነው ችግሩ መከሰቱ ሳይሆን፣ ጥንዶች በተፈጠረው ችግር ዙሪያ በግልፅ ተወያይተው መፍትሄ ለማፈላለግ ዝግጁ አለመሆናቸው ነው፡፡

sexual-dysfunction copy

በፍቅረኞችም ሆነ በባለትዳሮች መካከል የሚፈፀም ወሲብ፣ ለሁለቱም የእርካታ (የደስታ) ምንጭ መሆኑ ሲቀር ‹‹ለምን?›› ብለን መጠየቅም ሆነ ርዕሰ ጉዳዩን በጠረጴዛ ዙሪያ አምጥቶ አለመነጋገር ብዙዎቻችን አንደፍርም፡፡ ፈቃደኝነቱም የለንም፡፡ ችግሩ እየተባባሰ ሲመጣ፣ ግንኙነቱ በፍቅረኝነት ደረጃ ላይ ያለ ከሆነ በቃሽኝ (በቃኸኝ) በሚል ይቋረጣል፡፡ ትዳር ከሆነም የፍቺ ጥያቄ ማቅረብ በሀገራችን የተለመደና በየጊዜው ቁጥሩ እየጨመረ የመጣ ክስተት ሆኗል፡፡ የሚገርመው ግን በፍቅረኞች (በትዳር) ደረጃ የተመሰረተው ግንኙነት፣ በአንድ ጀንበር ለማፍረስ ሲወሰን እውነተኛው ምክንያት ከመጋረጃ ጀርባ የተደበቀ ነው፤፤ ፍቺ የጠየቀችው ሴቷ ከሆነች ‹‹ይሰክራል፣ ይደበድበኛል፣ ገንዘብ ይደብቀኛል፣ ከእኔ ሌላ ሴት ወዷል ወዘተ…›› በሚል የውሸት ጭንብል ትሸፍነዋለች፡፡ የትዳር ይፍረስ ጠያቂው ወንዱ ከሆነ ደግሞ ‹‹ትጨቀጭቀኛለች፣ ገንዘብ ታባክናለች፣ ከእኔ ይልቅ የምትሰማው ወላጆቿን ነው ወዘተ…›› በማለት ለግንኙነቱ መሻከር ቁልፍ ምክንያት የሆነውን ችግር ወደ ጎን ሲገፋው ይስተዋላል፡፡ ‹‹ችግሩን የደበቀ መድሃኒት አያገኝም›› እንደሚባለው፣ የስንፈተ ወሲብ ጉዳይን በሀገራችን ባህል ለውይይት የማይቀርብ አጀንዳ በመሆኑ፣ የብዙ ትዳሮችን መፍረስ ከመጋረጃ ጀርባ ያለ አብይ ምክንያት ሆኖ ዛሬም ድረስ ቀጥሏል፡፡

በዘርፉ ጥናት ያካሄዱ ሙያተኞች ስንፈተ ወሲብ መፍትሄ ያለው የስነ ልቦና፣ የአካላዊና የአዕምሯዊ ጤና ችግሮች ውጤት ነው ይላሉ፡፡ በዛሬው ዝግጅት የስንፈተ ወሲብ ችግር ምንነትን፣ መንስኤን፣ አጋላጭ ምክንያቶችን፣ በሀገራችንና በዓለም ላይ ያሉ አማራጭ መፍትሄዎችን እንደዚሁም ከርዕሰ ጉዳዩ ጋር በተያያዘ፣ መታወቅ አለባቸው በምንላቸው ሐሳቦች ዙሪያ፣ ሙያዊ ማብራሪያ እንደሚከተለው እናቀርባለን፡፡

ጥያቄ፡- ስለስንፈተ ወሲብ ችግር ምንነት፣ የተወሰነ አጠቃላይ ሐሳብ ብናነሳና ውይይታችንን በዚሁ ብንጀምረው ጥሩ ይመስለኛል?

ዶ/ር፡- ስንፈተ ወሲብ የሚለውን ቃል፣ ጠበብ ባለው ዐውዱ ሲታይ፣ የወንድም ሆነ የሴት ብልት አለመነቃቃትንና ለግንኙነት ዝግጁ ካለመሆን ጋር የቀጥታ ቁርኝት ያለው ነው፡፡ ነገር ግን ስንፈተ ወሲብ ብልት ለግንኙነት ዝግጁ አለመሆን ማለት ብቻ አይደለም፡፡ ከዚህም ሰፋ ያለ ትርጓሜ ያለው ነው፡፡ የስንፈተ ወሲብ ችግር በሁለት መንገድ የሚከሰት ነው፡፡ የመጀመሪያው ተፈጥሯዊ በሆነ የአፈጣጠር ችግር ማለትም በክሮሞዞን፣ የሴትነትና የወንድነት መገለጫ በሆኑት የኦቫሪና የቴስትሮን አፈጣጠር ችግር ምክንያት የሚፈጠር ሲሆን፣ ሁለተኛው ከውልደት በኋላ በዕድገት ሂደት በአካላዊ፣ በአዕምሯዊ፣ በስነ ልቦናዊና በአካባቢያዊ ምክንያቶች የሚፈጠር የስንፈተ ወሲብ ችግር ነው፡፡ በዚህ ወቅት የሚፈጠረው ችግር ለግብረ ስጋ ግንኙነት ፈፅሞ ዝግጁ አለመሆንን፣ ጭራሹኑ ስሜት ማጣትን፣ ፍላጎት አለመኖርን፣ የመጨረሻው እርካታ ላይ አለመድረስን፣ የሌላኘውን ስሜት ሳይጠብቁ ፈጥኖ መርካትን፣ ለግንኙነት ዝግጁ ያለመሆንን ሁሉ ያጠቃልላል፡፡

ጥያቄ፡- በተፈጥሮም ሆነ ከውልደት በኋላ የሚከሰተው የስንፈተ ወሲብ ችግር፣ በወንዶችም ሆነ በሴቶች ተመሳሳይ ነው ማለት ይቻላል?

ዶ/ር፡- በወንዶችና በሴቶች ላይ የሚከሰተው የስንፈተ ወሲብ ችግር አንድና ተመሳሳይ ነው ማለት ግን አይደለም፡፡ ለምሳሌ በተፈጥሮ ሴት ሁና የተፈጠረች ቢሆንም፣ ወንድ የመሆንና ሴትን ለማግባት የመፈለግ በሌላም በኩል በአንድ ሰው ላይ የሴትነትና የወንድነት ብልቶች በአንድ ላይ በመፈጠር ምክንያት የስሜት መሳከር በሁለቱም ፆታዎች፣ በተመሳሳይ መልኩ የሚከሰትበት አጋጣሚ እንዳለ መገንዘብ ተገቢ ይሆናል፡፡

ከውልደት በኋላ ከሚፈጠር የወሲብ ችግሮች አንፃር ሲታይ፣ በግብረ ስጋ ግንኙነት ጭራሹኑ ስሜትም ሆነ ፍላጎት ማጣት ብዙውን ጊዜ በሁለቱም ፆታዎች ላይ ይከሰታል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ የወሲብ አካል አለመነቃቃት (ዝግጁ ያለመሆን) ችግር በስፋት በወንዶች ላይ የሚታይ ሲሆን፣ ከሚፈፀመው የወሲብ ግንኙነት እርካታ (ደስታን) ማጣትና የመጨረሻው እርካታ ላይ አለመድረስ ሁለቱም ፆታዎች ይጋሩታል፡፡

ሴቶችም ቀደም ሲል ከነበራቸው ጥሩ ያልሆነ የወሲብ ግንኙነት ምክንያት ወሲብ ለመፈፀም ይፈራሉ ወይም ከነጭራሹ ግንኙነቱን ሊጠሉት ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም በፍቅር ከማይመርጡት ሰው ጋር ትዳር የመሰረቱ ሴቶች ወሲብ የደስታ ምንጭ ሳይሆን እንደ አንድ ስራ ይመለከቱታል፡፡ በመሆኑም ከግንኙነቱ እርካታን አይጠብቁም፡፡ ይህ ሁኔታ በወቅቱ ካልተፈታ ወደ ስር የሰደደ ስነ ልቦናዊ ችግርነት መሸጋገሩ አይቀርም፡፡

ጥያቄ፡- የችግሩ መንስኤ ምንድነው ይላሉ?

ዶ/ር፡- የስንፈተ ወሲብ መከሰቻ ምክንያቶች እነዚህና እነዚያ ብቻ ናቸው የሚባልበት አይደለም፡፡ የችግሩ መንስኤ ከወሲብ መፈፀሚያ አካላት ለውጦች እስከ ስነ ልቦናዊ ቀውሶች ድረስ የሚዘልቅ ነው፡፡ ለዚህም ነው የስንፈተ ወሲብ ችግር መምጫ ምክንያቶች አንድና አንድ የሚባሉ ሳይሆን ድርብርብ ናቸው የሚባለው፡፡

አንዱና ዋናው ምክንያት፣ አካላዊ የጤና ችግሮች ማለትም በአደጋ ምክንያት ወገብ አካባቢ መሰበርና እሱን ተከትሎ የሚከሰት የነርቭ ስርዓት መቃወስ፣ የኩላሊት፣ የጉበት፣ የስኳር፣ የደም ግፊት፣ የካንሰርና የልብ በሽታዎች በተጨማሪም በወንዶች የዘር ፍሬ ማመንጫና በሴቶች የእንቁላል ማኳቻ አካባቢ የሚፈጠሩ የተለያዩ አካላዊ በሽታዎች፣ የደም ስር ችግሮችና የኮሌስትሮል መጠን መጨመር ለስንፈተ ወሲብ ችግር መከሰት መንስኤ ይሆናሉ፡፡ ሌላው መንስኤ የስነ ልቦና መዛባት (መቃወስ) ነው፡፡ ስነ ልቦናዊ መዛባቱ በውጥረት፣ በጭንቀት፣ በድብርት፣ በጫና ውስጥ በመውደቅ፣ በፍርሃትና ከአይናፋርነት ጋር የተያያዙ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከስነ ልቦና ምክንያቶች ቀጥሎ ለስንፈተ ወሲብ ችግር መከሰት፣ ከአዕምሮ ጀምሮ እስከ ታችኛው ቅርንጫፍ የነርቭ ስርዓት ድረስ ያለው አካባቢ በከፊል አልያም ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ፣ የነርቭ ስርዓት ጤና መቃወስ ካለ ለችግሩ መከሰት በቂ ምክንያት ይሆናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የወንድ ብልት ለግብረ ሥጋ ግንኙነት ዝግጁ መሆን የሚችለው፣ የታችኛው የወንድ ብልት ክፍል በደም ሲሞላ ነው፡፡ ነገር ግን የደም ስሮች በተለያየ ምክንያት ችግር ውስጥ ሲወድቁ በቂ የደም መጠን ወደ ወንዱ ብልት አይደርስም፡፡ ካልደረሰ ደግሞ የወንድ ብልት ተነቃቅቶ ለወሲብ ዝግጁ የሚሀንበት ዕድል የለም ማለት ነው፡፡

ቴስቴስትሮን የተባለው ስሜት ቀስቃሽ ሆርመን፣ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሥራውን በአግባቡ መስራት ሳይችል ሲቀር፣ በብልት አካባቢ በሚሰራ ቀዶ ህክምና ሳቢያ እዚያ አካባቢ ያሉ ነርቮችና ደም ስሮች ሲጎዱ እንዲሁም ለረጅም ጊዜ ባይስክል መንዳት ለስንፈተ ወሲብ ችግር ያጋልጣል፡፡ በሌላኛው ገፅ ደግሞ ሌሎች ህመሞችን ለመፈወስ ተብለው የሚሰጡ መድሃኒቶች ለአብነት የደም ግፊት፣ ለአዕምሮ ህመም፣ ለጨጓራ፣ ለሽንት መሽናት፣ የኮሌስትሮልን መጠን ዝቅ ለማድረግ የሚወስዱትና ለሌሎች የጤና ችግሮች የምንወስዳቸው መድሃኒቶች፣ ለስንፈተ ወሲብ ችግር መከሰት መንስኤም የመሆን ዕድል አላቸው፡፡ በተለይም ከ25 በመቶ በላይ የሚሆነው የወንዶች የስንፈተ ወሲብ ችግር ምክንያቶች፣ ለሌሎች ህመሞች ተብለው ከሚሰጡ መድሃኒቶች ጋር ይቆራኛል፡፡ ከ10 እስከ 20 በመቶ የሚሆነው ምክንያት ስነ ልቦናዊ ሲሆን፣ ከ40 እስከ 80 በመቶ የሚሆነው የስንፈተ ወሲብ ችግር ከአካላዊ ጤና ጋር የተያያዘ በቂ ምክንያቶች አሉት፡፡

ከላይ በስንፈተ ወሲብ መከሰት በምክንያትነት ከተዘረዘሩት ውጭ በመጠኑ የበዛ አልኮል መውሰድ፣ ሲጋራ ማጨስና ለመዝናኛ ተብለው የሚወሰዱ ሱስ የማስያዝ አቅም ያላቸው መድሃኒቶች ሁለቱንም ፆታዎች ለስንፈተ ወሲብ ችግር ያጋልጣቸዋል፡፡ ሌላውና ለስንፈተ ወሲብ መፈጠር እንደ አንድ ምክንያት መገለፅ ያለበት፣ ሰውነትን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ሽባ የሚያደርገው ፓርኪንሰን የተባለው በሽታ ነው፡፡

ጥያቄ፡- የስንፈተ ወሲብ ችግር በሀገራችንና በዓለም አቀፍ ደረጃ በምን ሁኔታ ላይ የሚገኝ ነው?

ዶ/ር፡- ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ አድማሱንና መጠኑን በማስፋት ላይ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በአሜሪካ ማቹሲስተስ ሆስፒታል የተደረገው ጥናት እንዳመላከተው፣ ከ40 እስከ 70 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሰዎች 52 በመቶ፣ በድህነት ውስጥ ያሉ 14 በመቶ፣ ትዳር የፈቱ 14 በመቶና የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰዎች 13 በመቶ ለችግሩ የመጋለጥ ዕድል ይኖራቸዋል፡፡ በቦስትሰን የተካሄደ ሌላ ጥናት እንዳመለከተው ደግሞ 30 ሚሊየን የሚሆኑ የስንፈተ ወሲብ ችግር ያለባቸው ወንዶች በአሜሪካ ብቻ ይኖራሉ፡፡ በጥናቱ ውስጥ ከተካተቱና ዕድሜያቸው 70 ዓመት ከሞላቸው ወንዶች ደግሞ 70 በመቶ የሚሆኑት የስንፈተ ወሲብ ችግር እንዳለባቸው ተረጋግጧል፡፡

የስንፈተ ወሲብ ችግር በሀገራችን በምን ደረጃ ላይ እንዳለ የሚያመለክት ጥናት ማግኘት ባለመቻሉ፣ የችግሩን ስፋት በአግባቡ መገንዘብ አልተቻለም፡፡ ነገር ግን ጤና ተቋማትን መሰረት አድርገው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ የስንፈተ ወሲብ ችግር በአገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ በመሄድ ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ በየዓመቱ ግልፅ ምክንያት ሳይቀመጥላቸው የሚፈርሱ ትዳሮች እየጨመሩ እንደሆነ የሚያሳዩ መረጃዎች አሉ፡፡ በኤዢያ፣ በላቲን አሜሪካ፣ በደቡብ አፍሪካና በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ትዳርን የሚያናጉ ምክንያቶችን ለማወቅ በተጠኑ ጥናቶች ከ65 በመቶ በላይ የሚሆነው ምክንያት አንደኛው ወገን ሌላኛውን በወሲብ ግንኙነት ወቅት መርዳት ካለመቻሉ (ካለማስደሰቱ) ጋር የተያያዘ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በሀገራችን በግልፅ የወጣ ምክንያት ሳይኖራቸው የሚፈርሱም ሆነ በግጭት የሚናጡ ትዳሮች ሁሉም ባይሆኑ አብዛኞቹ ምክንያታቸው የስንፈተ ወሲብ ችግር እንደሆነ ይገመታል፡፡

የስንፈተ ወሲብ ችግር የስነ ልቦና፣ የአዕምሮና የአካላዊ ጤና ችግር ብቻ ሳይሆን፣ ከግለሰቡ እስከ ቤተሰባዊ ሕይወት ድረስ የሚዘልቅ ማህበራዊ ችግርም ጭምር ነው፡፡ አንደኛው ወገን በስንፈተ ወሲብ ችግር ውስጥ አለ ማለት ሌላኛው ወገንም ተጠቂ ከመሆን የሚያመልጥ አይሆንም፡፡ እንዲህ ያለው ሁኔታ ደግሞ የትዳር መፍረስንና የልጆችን መበተን ያመጣል፡፡ ልጆቹን የሚረዳቸው ቤተሰብ ከሌላ ለረሃብና ለእርዛት ይጋለጣሉ፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ በስንፈተ ወሲብ ችግር ሳቢያ ከፈረሱ ትዳሮች የተገኙ ልጆች የማህበረሰቡ ችግር ወደ መሆን ተሸጋገሩ ማለት ነው፡፡

ጥያቄ፡- ችግሩ ያለበት ሰው ከሚያሳያቸው ምልክቶች ዋና ዋና የሚባሉትን ቢገልፁልኝ?

ዶ/ር፡- ወንዶችም ሆኑ ሴቶች የስንፈተ ወሲብ ችግር ሲከሰትባቸው፣ በጋራ ወይም በተናጠል ከሚያሳዩዋቸው ምልክቶች ዋና ዋና ተብለው የሚታወቁት ቀጥሎ የምገልፃቸው ናቸው፡፡

– የወሲብ ፍላጎት ማጣት (ለሁለቱም)

– የወሲብ መፈፀሚያ አካላት ለወሲብ ዝግጁ አለመሆን (በወንዶች)

– ለግንኙነት ዝግጁ የሚያደርግ ፍሳሽ በበቂ መጠን አለመመንጨት፣ የሚደረገውን የወሲብ ግንኙነት ደረቅና ህመም የበዛበት ያደርገዋል (ለሴቶች)

– የመጨረሻው የእርካታ ደረጃ ላይ አለመድረስ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ የስንፈተ ወሲብ ምልክቶች ናቸው ተብሎ ይወሰዳል፡፡

ጥያቄ፡- አንዳንድ ሰዎች የስንፈተ ወሲብ ችግርን ፈጥኖ እርካታ ላይ ከመድረስ በተጨማሪም ከወንዶች ብልት ማነስና ከሴቶች ብልት መስፋት ጋር ሲያያይዙት ይታያል፣ ይህ አስተሳሰብ ሳይንሳዊ መሰረት አለው ማለት ይቻላል?

ዶ/ር፡- የተጠቀሱ ጉዳዮች ከስንፈተ ወሲብ ጋር የሚያያዙ አይደሉም፡፡ በእርግጥ ፈጥኖ የዘር ፍሬን የማፍሰስ ችግር ያለባቸው በርካታ ቁጥር ያላቸው ወንዶች እንዳሉ ግልፅ ነው፡፡ የዚህ ምክንያቱ ለወሲብ ጉጉ መሆን፣ ዘር ፍሬዬ ፈጥኖ ሊፈስብኝ ነው ብሎ መጨነቅና ተጣማሪዬና በወሲብ ማርካት አልችልም በሚል ስሜት ዝግጁ አለመሆን ጋር የተያያዙ ችግሮች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እንዲህ ያሉ ሰዎች የስነ ልቦና ሙያተኛ ምክር ከተደረገላቸው በቀላሉ ከችግራቸው የሚላቀቁበት ዕድል ሰፊ ነው፡፡ ፈጥኖ የዘር ፍቼን ማፍሰስ ከላይ ከዘረዘርናቸው ምክንያቶች ሌላጋር የሚተሳሰሩበት ሁኔታም እንዳለ መገንዘብ ይገባል፡፡ በሌላም በኩል የወንድ ብልት ማነስም ሆነ የሴት ብልት የመስፋት ጉዳይ፣ ለስንፈተ ወሲብ ችግሮች ጋር የሚያስተሳስረው ምንም አይነት ምክንያት እንደሌለው በመገንዘብ አጠረብኝ ብሎ መጨነቅን ማስወገድ ጠቃሚ ይሆናል፡፡ ሰፋብኝ ብሎ ከመሸማቅም ራስን ነፃ አድርጎ በነፃነት ስሜትን ሰጥቶ፣ ስሜትን ለመቀበል ዝግጁ መሆን አስፈላጊ ይሆናል፡፡

ጥያቄ፡- ችግሩን ለይቶ ለማወቅ ተግባራዊ የሚደረጉ ምርመራዎች የትኞቹ ናቸው?

ዶ/ር፡- ትልቁና የመጀመሪያው ምርመራ ሐኪሙ ከበሽተኛው ጋር ስለ ህመሙ አጠቃላይ ሁኔታ በቂ መረጃ ለማግኘት የሚያደርገው ጥልቅ ውይይት ነው፡፡ በውይይቱ የተገኘውን መሰረት በማድረግ የደም፣ የሽንት፣ የሆርሞንና ተያያዥነት ያላቸው ምርመራዎች ይካሄዳሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በኤምአርአይ እና በሌሎችም ቴክኖሎጂ አመጣሽ መሳሪያዎች፣ የስንፈተ ወሲብ ችግሩን በትክክል መኖሩን እንዲሁም የችግሩን ስፋትና አይነት በትክክል ለይቶ ለማወቅ የሚያስችል ምርመራ እናደርጋለን፡፡

ጥያቄ፡- ለመሆኑ የስንፈተ ወሲብ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሳይንሳዊ መፍትሄዎች ካሉ ቢገልፁልኝ?

ዶ/ር፡- የመጀመሪያው አማራጭ መፍትሄ በስነ ልቦና ባለሙያ በተጋገዝ ጭንቀትን፣ ፍርሃትን፣ ውጥረትን፣ ድብርትን፣ ስጋትንና ቀድሞ ተሸናፊ የመሆን ስነ ልቦናዊ ችግሮችን ማስወገድ ይቻላል፡፡ ለዚህ ችግር መፍትሄ የሚሰጡ ሳይኮሎጂካል ቴራፒዎች አሉ፡፡ ስለሆነም የስነ ልቦና ባለሙያዎችን ምክር ተቀብሎ በመተግበር፣ ህክምናውን በአግባቡ መፈፀም ከተቻለ በአጭር ጊዜ ውስጥ አስተማማኝ መፍትሄ ማግኘት ይቻላል፡፡ በዚህ ሂደት ደስተኛ የመሆንና በራስ የመተማመን መንፈስም በዚያው መጠን ይዳብራል፡፡ ነፃነት ያለው፣ ከስጋትና ከጭንቀት የፀዳ ግንኙነት በመፈፀም የመጨረሻው እርካታ ላይ የሚደርስበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ጠብቆ ለመዝለቅም የሁለቱን ጥንዶች በአግባቡ ለመደጋገፍ የሚያስችል የቅንነት ባህልን እንዲገነቡ ያስፈልጋል፡፡ ከስነ ልቦናዊ መፍትሄዎች ባሻገር ለስንፈተ ወሲብ ችግር መከሰት ምክንያት ናቸው ብለን ያነሳናቸውን በሽታዎች፣ ለምሳሌ ስኳርንና ደም ግፊትን በአግባቡ በቁጥጥር ስር ማዋል እንዲሁም ሌሎችን የውስጥ ጤና ችግሮችን ጊዜ ሳይወስዱ መታከም ተገቢ ይሆናል፡፡ ለሌሎች በሽታዎች ተብለው የሚሰጡ መድሃኒቶችን በተቻለ አቅም ማስወገድ ይገባል፡፡ በሌላም በኩል የስንፈተ ወሲብ ችግርን በጊዜያዊነት ቢሆን መፍትሄ ለመስጠት የሚችሉ መድሃኒቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ ሲልደናፊል (በንግድ ስያሜው ቪያግራም)፣ ቮርድናፍና ታላፌን የሚባሉት በዓለም ላይ የሚታወቁ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ሲልደናፊል (በንግድ ስያሜው ቪያግራም) የሚባለው መድሃኒት በሀገራችንም ይገኛል፡፡ ይህ መድሃኒት በዋጋው ተመጣጣን የሚባል ነው፡፡ እዚህ ላይ ማንኛውም ሰው መገንዘብ ያለበት፣ መድሃኒቱ መወሰድ ያለበት ሌሎች ስነ ልቦናዊ ችግሮችን ለማስወገድና መፍትሄ ማምጣት ሳይቻል ሲቀር ብቻ ይሆናል፡፡

ሌላው አማራጭ ህክምና፣ በሆርሞን እጥረት የተነሳ የስንፈተ ወሲብ ችግር ለአጋጠማቸው ሰዎች፣ የሆርሞን መተኪያ ህክምና ይሰጣቸዋል፡፡ ይህ የህክምና ዘዴ በሀገራችንም የሚሰጥ ነው፡፡ ከላይ በገለጽናቸው አማራጭ ህክናዎች መፍትሄ ላላገኙ ሰዎች፣ ምንም እንኳን የህክምና ዘዴዎች በሀገራችን ባይገቡና ጥቅም ላይ ባይውሉም በሌላው ዓለም የሚሰራባቸው ሌሎች ተጨማሪ መፍትሄዎች አሉ፡፡

– ቫኪዩም ዲቫይስ የሚባል ዘዴ አለ፤ ይህ ዘዴ የወንድ ብልት እንዲቆም በማድረግና ቫኪዩም ዲቨይሱን ብልት ላይ በመግጠም ወዲያውኑ ውጤታማ ግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈፀም ያስችላል፡፡

– ብልት በበቂ መጠን ወሲብ መፈፀም እንዲችል የተነቃቃና ለወሲብ የተዘጋጀ፣ የወንድ ብልት ላይ የሚወጉ መድሃኒቶች በዓለም ገበያ ላይ አሉ፡፡

– ውጤታቸው አስተማማኝነቱ የሚያጠራጥር በመሆኑ፣ የጎንዮሽ ጉዳታቸው ጠንካራ ስለሆና አንዳንድ ጊዜ ተመልሶ የማይተኛ የብልት መቆምን የሚያመጡ በመሆናቸው፣ አማራጭ ካልጠፋ በስተቀር ጥቅም ላይ አይውሉም እንጂ በሽንት ቧንቧ ወደ ውስጥ የሚጨመሩ የስንፈተ ወሲብ ችግር መድሃኒቶች በሌሎች የዓለም ሀገሮች በስፋት ይሸጣሉ፡፡

– በቀዶ ህክምና ብልትን በመሰንጠቅ፣ ሰው ሰራሽ በሆነ መንገድ ማቆሚያ በማስገባት፣ ውጤታማ ወሲብ መፈፀም የሚያስችል ዘዴ ነው፡፡

– የስንፈተ ወሲብ ችግሩ ዋነኛ መንስኤ በደም ስር ላይ የተከሰተ የጎላ ጉዳት መሆኑ በምርመራ ከተረጋገጠ፣ ደም ስሮቹን በማይክሮ ሰርጀሪ የማስተካከልና ጤናማ የሚያደርግ የህክምና ዘዴም በሌላው ዓለም ወደ ተግባር ከተሸጋገረ ከርሟል፡፡

ጥያቄ፡- አንዳንድ ሰዎች ያለ ሐኪም ትዕዛዝ ቪያግራምንም ሆነ ሌሎች መድሃኒቶችን በራሳቸው ሲወስዱ ይስተዋላል፣ እንዲህ ያለው ተግባር ችግር አያስከትልም?

ዶ/ር፡- ቪያግራም ማንኛውም ሰው የሚወሰደው መድሃኒት አይደለም፡፡ መድሃኒቱ የስኳር፣ የደም ግፊት፣ የልብና የኩላሊት በሽታዎችን ያባብሳል፡፡ እንደዚሁም የደም ስሮችን በማጥበብ ስትሮክንና ደም ማነስን ያመጣለ፡፡ እነዚህ የጤና ችግሮች ያሉባቸው ሰዎች በምንም ምክንያት ቪያግራን መውሰድ የለባቸውም፡፡ ስለሆነም በምንም መንገድ ቢሆን ቪያግራም ያለ ሐኪም ትዕዛዝ መወሰድ የለበትም፡፡ መድሃኒቱ በሐኪም ትዕዛዝ ቢሆንም ለረጅም ጊዜ ከተወሰደ ሱስ የመሆን ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ ሱስ ከሆነ መድሃኒቱ ካልተወሰደ በስተቀር ወሲባዊ ግንኙነት መፈፀም የማይቻልበት ደረጃ ላይ ያደርሳል፡፡ ሌሎችም መድሃኒቶች ተመሳሳይ የሆነ የጎንዮሽ ጉዳት ስላላቸው በተቻለ አቅም አግባብ ያለው ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

ጥያቄ፡- ለማጠቃለያ ማንሳት የሚፈልጉት ሐሳብ ካለ ያንሱትና እንሰነባበት?

ዶ/ር፡- የስንፈተ ወሲብ ችግር ሊታከምና ሊድን የሚችል የጤና ችግር መሆኑን ሁሉም ሰው ቢገነዘብ ጠቃሚ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ሁለቱ ተጣማሪች የተሰማቸውን ጥሩ ያልሆነ ስሜት ከደመባበቅና ወደ ተባባሰ የስነ ልቦና ችግር ከማምራት ይልቅ በግልፅ መነጋገር ይኖርባቸዋል፡፡ መፍትሄ ባለው ችግር ግንኙነታቸውን ጤናማ ወዳልሆነ አቅጣጫ መምራት አይኖርባቸውም፡፡ ስለሆነም በተፈጠረው ችግር ዙሪያ መደማመጥና መከባበር በሰፈነበት አግባብ፣ የመነጋገር ልምድን ማዳበር ይጠበቅባቸዋል፡፡ የስንፈተ ወሲብ ችግር ከተከሰተ በኋላ ማከም ብቻ ሳይሆን ችግሩን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ ዘዴዎችም እንዳሉ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ ለአብነት ጭንቀትን፣ ድብርት፣ መረበሽንና ፍርሃትን መቀነስ ከተቻለም ጭራሹኑ ማስወገድ ይገባል፡፡ በተጨማሪም አልኮልን አዘውሮ ከመውሰድ መታቀብ፣ ጫት መቃምና ሲጋራ ማጨስን በተቻለ መጠን ማስወገድ ያስፈልጋል፡፡ በተፈጥሮ የተከሰተ የስንፈተ ወሲብ ችግር መኖን አለመኖሩን ለማረጋገጥ፣ ልጆች 18 ዓመት ሳይሞላቸው ቢመረመሩና ችግሩ ካለ ቢታከሙ ጠቃሚ ይሆናል፡፡

Health: በኢስላም ማህፀንን ማከራየትና መከራየት እንዴት ይታያል? –ዳኢ መንሱር ሁሴን ይነግሩናል

$
0
0

ዳኢ መንሱር ሁሴን ስለ ማህፀን ማከራየት ከኢስላም አስተምህሮ አንፃር እንደሚከተለው አብራርተውልናል፡፡

ምስጋና ለአሏህ (ሱ.ወ) የተገባ ነው፡፡ ሶላትና ሰላም በአሏህ መልዕክተኛ በሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ ይስፈን፡፡
ወደ ዋናው ርዕሳችን ከመግባታችን በፊት እንደ ኢስላም አስተምህሮ የሰው ልጆች የተፈጠሩባቸውን አራት መንገዶች እንመልከት፡፡

የመጀመሪያው መነሻችን የሆኑት የአባታችን አደም (ዐ.ሰ) አፈጣጠር ሲሆን፣ እርሳቸውም ያለ እናትና አባት በአሏኅ ችሎታና ጥበብ ከአፈር መፈጠራቸው ነው፡፡ በመቀጠልም እናታችን ህዋ ደግሞ ያለ ሴት ከአባታችን አደም ጎን ተፈጠሩ፡፡ በሶስተኛ የምናገኘው የነቢዩሏህ ዒሳ (ዐ.ሰ) ከእናት ብቻ ያለ አባት በአሏህ (ሱ.ወ) የ‹‹ሁን›› ቃል የተወለዱበት ተአምራዊ አፈጣጠር ነው፡፡ በመጨረሻ የምናገኘው ብዙሃኑ የአደም ልጆች ከእናትና አባት የተወለድን የምንራባበት መንገድ ነው፡፡
የሰው ልጆች ምድር ላይ የተገኘንባቸውን መንገዶች ካየን፣ በርዕሳችን ስላነሳነው ልጅ ምናልባትም ከሶስት ወላጆች እንዲገኝ ‹‹ሰለጠንኩ›› የምትለው ዓለም ስላመቻቸችው፣ ‹‹የማህፀን ኪራይ›› ኢስላም የሚለውን ትንሽ እንበላችሁ፡፡
እንደሚታወቀው ይህ ጉዳይ፣ በቀደሙት ጊዜያቶች የማይታወቅና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተጀምሮ ዓለም ላይ እየተስፋፋ ያለ ነገር ነው፡፡ ከዚህ በፊት ስላልነበረ ቀደምት የኢስላም ምሁራን በጉዳዩ ላይ የተናገሩት ነገር የለም፡፡ በተጨማሪም ታዋቂ የሙስሊሙ ማህበረሰብ መሪዎች (የመዝሃብ ባለቤቶች) የነበሩ፣ ይህን ጉዳይ በኢስላም መፈቀዱን ወይም አለመፈቀዱን የዘገቡትም የተናገሩትም ነገር የለም፡፡
pregnancy-facts04
እዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባን ነገር ቢኖር፣ የሙስሊሙ የመዝሃብ መሪዎች ከቁርአን እና ከሐዲስ (የነብዩ ሙሐሙድ አስተምህሮ) ባገኙት ትንተና ሰጥተዋል፡፡ ይህ አይነቱ ትንታኔ ደግሞ ከቁርአን እና ከሐዲስ ቀጥሎ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ሕይወቱንም እዚያ ላይ ባገኘው ሕግ ነው የሚመራው፡፡
ለዚህም ነው ከላይ በጉዳዩ ላይ ከነርሱ የተገኘ ማብራሪያ አለ? ወይስ የለም የሚለውን ለማስቀመጥ የሞከርነው፡፡ እነሱ የሰጡት ትንታኔ የለም ማለት ግን ኢስላም ስለዚህ ጉዳይ የሚሰጠው ብያኔ የለም ማለት አይደለም፡፡ አሏህ (ሱ.ወ) ከቁርአኑ ላይ እንዲህ ብሏል፡-
‹‹በመጽሐፉ (በቁርአን) ውስጥ ምንም (ስለምንም) ነገር (ሳንገልፅ) አልተውንም›› (አል አንአም 38) በሌላ ምዕራፍ ላይም፣ ‹‹ዕውቀቱ ከሌላችሁ የዕውቀት ባለቤቶችን ጠይቁ›› (አል አንቢያእ 7)
ይህ ማለት፣ የትኛውም አዲስ ነገር ቢፈጠር የሚፈጠረው ነገር ጠቅለል ብሎ በተቀመጠው የአሏኅ (ሱ.ወ) ቃል (ቁርአን) እና የመልዕክተኛው ንግግር (ሐዲስ) ሕግ ስር በጊዜው በሚኖሩ ምሁሮች ጥልቅ እይታ እና ግንዛቤ በሚኖሩ ምሁሮች ጥልቅ እይታ እና ግንዛቤ መሰረት ተገቢ የሆነ ትንተና እና ብያኔ ይሰጥበታል፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው፣ ይህ ጉዳይ መጤ ከመሆኑም ጋር አንዳንድ ሰዎች ስለ ጉዳዩ ሰፊ ጥናት ሳያደርጉ፣ በደፈናው ችግር እንደሌለውና ለሰዎች ጥሩ የሕይወት መቀጠያ ዘዴ አድርገው ይገልፁታል፡፡ ነገር ግን ይህ አመለካከት እንደማያዋጣና ጉዳዩን ትኩረት ሰጥተን ልናየው እንደሚገባ በዚህ ጽሑፍ ለመጠቆም እንሞክራለን፡፡
ማህፀንን ስለማከራየትም ሆነ መከራየት አሁን ላይ ያሉ ሙስሊም ምሁራ የሰጡትን ትንታኔ እና ብያኔ ከማየታችን በፊት አላህ (ሱ.ወ) ስለ ሀፍረተ ገላችን ምን እንደተናገረ አጠር ባለ መልኩ እንመልከት፡፡
አንደኛ፡- ‹‹(አማኞች) እነዚያ ብልቶቻቸውን (ከሐራም) የሚጠብቁት…›› (አል ሙእሚኑን፤ 5-6)
ከአንቀፁ እንደምንረዳው፣ አላህ (ሱ.ወ) አንድ ወንድ በሸሪዓዊ መንገድ ከተፈቀደችለት ሴት ውጭ የሚያደርገውን የግብረ ሥጋ ግንኙነት እርም አድርጓል፡፡
ሁለተኛ፡- አሏህ (ሱ.ወ) የሰውን ልጆች ዘራቸውን እና ልጆቻቸውን እንዲጠብቁ አደራ ብሏል፡፡

ሀፍረተ ገላችንን እና ክብራችንን እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በአጭሩ ይህን ካልን፣ ወደ ዋናው ርዕሰ ገዳይ ስንገባ ማህፀን ማከራየት ካለምንም የሐሳብ ልዩነት በኢስላም ክልክል (ሐራም) ነው ይሉናል- ሙስሊም በኢስላም ክልክል (ሐራም) ነው ይሉናል- ሙስሊም ምሁራኑ፡፡ ለዚህም የሚከተሉትን ምክንያቶች ያቀርባሉ፡፡

1. የሚወለደው ልጅ የእናት፣ የአባት ብሎም የዘር እውቅናን ሙሉ በሙሉ ይህ ነው ለማለት ብዥታ ውስጥ ይከተላል፡፡ ይህ ብዥታ በኪራይዋ እናት እና በዋናዋ እናት መካከል ወደ ፀብ ይወስዳል፡፡ የሚወለደው ልጅ ከሁለቱ እናቶች የአንዷ እንደሆነ እርግጠኛ ብንሆንም፣ በእርግጠኝነት የዚህች ነው ብሎ መወሰን ግን አንችልም፡፡ ከሳይንሱም ጋር ተያይዞ በዘርፉ ሰፊ ጥናት ያደረጉት ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች ስለ ችግሩ ብዙ የሚሉት ስላለ ያንን ፈልጎ መረዳት ከእኛ የሚጠበቅ ይሆናል፡፡ ስለዚህ እንደ ኢስላም ህብረተሰቡ ይህን እንዲርቀው ይመከራል፡፡

2. ይህን ጉዳይ ከወንዱ ፍትወት እንዲሁም ከሴቷ እንቁላል ለመውሰድ ሂደቱ የእሷንም የሱንም ሀፍረተ ገላ ማየት ይጠይቃል፡፡ በተጨማሪም የኪራይዋ እናት ሀፍረተ ገላን ማየት ግድ ይላል፡፡ ይህ ደግሞ ከላይ ከተጠቀሰው የኢስላም አስተምህሮ ጋር ይጋጫል፡፡ የሌላን ወገን ሀፍረተ ገላን ማየት ክልክል ስለሆነ (ባል የሚስትን ሚስት የባልን ሐፍረተ ገላ ማየት ሲቀር)

ይህን በተመለከተ አሏህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡- ‹‹ለአማኝ ወንዶች እይታቸውን እንዲቆጣጠሩና ብልቶቻቸውንም እንዲጠብቁ ንገራቸው›› (አን ኑር 30)
ይህም አንዱ የሌላውን ሀፍረተ ገላ አይመልከት፡፡ ለዚያም እይታውን ወደ ታች ይመልስ፣ የራሱንም ሀፍረተ ገላ ይሸፍን ማለት ነው፡፡ ከፊል ሙስሊም ምሑራን በጣም ለከፋ ችግር ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ፣ (ሴት ከሆነች አባቷ፣ ባሏ፣ ለአቅመ አዳም የደረሰ ወንድሟ ወይም ልጇ ባሉበት) መታየት እንደሚቻል ብይን ይሰጣሉ፡፡
ይህ አይነቱ ጥንቃቄ ያስፈለገውም፣ ሰይጣን የሰው ልጆች ከአምላካቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማቋረጥ የራሱ ግብረ አበሮች እንዳያደርጋቸው በማሰብ ነው፡፡ ተቃራኒ ፆታዎች ከተፈጥሮ መሳሳቡ ጋር የሰይጣን ጉትጎታ ሲጨምር፣ ህገ ወጥ የሆኑ መነካካትና መተያየት ወደ ዝሙት እንዳያመራቸው ነው፡፡

3. የማህፀን ኪራይ የምዕራቡ ዓለም ‹‹ስልጣኔ›› የፈጠረው ግኝት ነው፡፡ በተለይ ከሃይማኖት ህግጋት አንፃር ስልጣኔቸው ደግሞ በከፊል ሰይጣኔ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ኢስላም ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ጋር ሰፊ ግንኙነት ቢኖረውም ሰዎች ከተፈጠሩለት አሏህን የማምለክና ለትዕዛዙ እጅ የመስጠት አላማ ጋር የሚያጋጭን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውጤት አያስተናግድም፡፡

ጠቅለል ባለ መልኩ፣ በስልጣኔ ስም ሁሉንም መከተል ሳይሆን ጥሩና መጥፎ ጎጂና ጠቃሚውን ለይተን ልንጠቀምበት እንደሚገባ ኢስላም ያስተምራል፡፡
ኢስላም እንደ እምነት፣ ለስነ ምግባርና ባህሪ በጥቅሉ ለመልካም ማህበራዊ እሴቶች ትልቅ ዋጋ ይሰጣል፡፡ በተቃራኒው ምዕራቡ ዓለም ደግሞ ለዚህ ጉዳይ ትኩረት ሲሰጥ አይታይም ይላሉ ምሁራኑ፡፡ ስለ ማህፀን ኪራይ ክልክልነት ለማስረዳት ከተነሱት ምክንያቶች፣ ማህበረሰባዊ ቀውሶችን ስለሚያስከትል ሸሪዓዊ (ኢስላማዊ ሕግ) መነሻ የለውም የሚል ነው፡፡ ይልቁንም ማህፀን የሴቷ ሀፍረተ ገላ ስለሆነ ለሕጋዊ ባሏ እንጂ ህጋዊ ባሏ ያልሆነ ወንድ ፍትወት ተቀብላ ልታሳድግበት አይፈቀድላትም፤ ሸሪዓ አምርሮ ይቃወመዋል፡፡

እንደ ኢስላም አንድ ወንድ ያላገባትን ሴት ባይተዋር ለሆነ እርግዝና የመጠቀም መብት የለውም፡፡ በሌላ አገላለፅ አንዲት ሴት ማህፀኗን ላላገባት ወንድ ስታከራይ ሀፍረተ ገላዋን በጋብቻ ላልተሳሰራት ወንድ እየፈቀደች ነው፡፡ እርሷም ለእርሱ እርሱም ለእርሷ ስለማይፈቀዱ ሙሉ ዝሙት ይሆናል ባይባልም ተግባሩ ግን ሙሉ በሙሉ ሐራም ነው፡፡
የእርሱን ፍትወት በእርሷ ውስጥ እንዲያሳድግ ከማድረጉም በላይ፣ ፅንሱ የሚመገበውና የሚያድገው በማህፀን ውስጥ ስለሆነ በጎም ሆነ መጥፎ ተፅዕኖ የሚያርፍበት ከኪራይዋ እናቱ ነው፡፡ ስለሆነም ይህቺ ሴት የጎጂ ልማዶች (መቃም፣ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት ወዘተ…) ተጠቂ ብትሆን ፅንሱ ከጅምሩ ገና ለአደጋ ተጋላጭ ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ሂደት ላይ ጽንሱን የሚከታተለው ዶክተር፣ ፅንሱ ላይ የአካል ጉዳት ይታያልና የወሊድ ጊዜሽ ከመድረሱ በፊት በቀዶ ጥገና ወጥቶ ጽንሱ መታከም አለበት ቢላት ፈቃደኛ ትሆናለች? የእኔ ለማትለው የሰው ልጅ ትክክለኛዋ እናቱ ብትሆን፣ ልታደርገው የምትችለውን የራሷን ሕይወት ቤዛ የማድረግ ጥያቄ ትቀበላለች?

እዚህ ላይ ሌላ ሳንጠቅስ የማናልፈው ሐሳብ ቢኖር፣ በሕጋዊ ባልና ሚስቶች መካከል በተፈጠረ አንዳች ውስጣዊ ችግር ምክንያት፣ ሚስቲቱ መፀነስ ካልቻለች በሕክምና ድጋፍ የባሏን ፍትወትና የራሷን እንቁላል ውጭ ላይ አሳድጎ ፅንሱን ወደ ራሷ ማህፀን አስገብተው ቢወልዱ የራሳቸው እስከሆነ ድረስ ችግር እንደሌለው ሙስሊም ምሑራን ይገልፃሉ፡፡
4. በእርግዝና ወቅት ያልተጠበቁ እንደ ስኳር፣ የደም ግፊት ያሉ ከባባድ ህመሞች የሚገጥሟቸው ሴቶች አሉ፡፡ እነኚህ በሽታዎች በአፋጣኝ ህክምና ካላገኙ የነፍሰ ጡሯን ህይወት ሊቀጥፉ ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም ፅንሱን ለመጠበቅ (ለማዳን) ቀዶ ህክምና (ኦፕራሲዮን) የግድ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሁን ኃላፊነትስ የሚወጣው ማን ነው? ይህቺው
የኪራይ እናት ወይስ የእንቁላሏ ባለቤት?

ከዚህ ሂደት ጋር ተያይዘው የተለያዩ እንግዳ ነገሮችም ሊከሰቱ ይችላሉ፡፡ እነዚህን የባህል፣ የስነ ልቦና እና ሌሎች ማህበራዊ ቀውሶች እንዴት ነው የምንፈታቸው? ኃላፊነቱን ለየትኛይቱ እናት እንስጣት?
ከዚህ በመነሳት አንድ ድምዳሜ ላይ እንደርሳለን፡፡ ይኸውም ፅሱ በዚያችው በእውነተኛ እናቱ ማህፀን አሏህ (ሱ.ወ) እንደፈቀደለት ይኑር፡፡ እናቱም ጽንሱን የመጠበቅና የመንከባከብና በአሏህ ፈቃድ ጊዜው ሲደርስም የመውለድ ሰብአዊ፣ ሃይማኖታዊና ህጋዊ ግዴታ ይኖርባታል፡፡
‹‹ማህጸን መከራየት ሞግዚት እንደመቅጠር ነው›› የሚሉ አንዳንድ ወገኖች አሉ፡፡ ፍየል ወዲያ… እንዲሉ፣ ይህ ጤነኛ አዕምሮ ሊቀበለው የማይችል ሐሳብ ነው፡፡ አንድን የተወለደ ልጅ ሞግዚት ብትንከባከበው፣ ጡቷን ብታጠባውና ብታሳድገው ልጁ በኪራይ ማህፀን እንደሚያድገው ፅንስ ያለ ተፅዕኖ አይገጥመውም፡፡ ከሞግዚቷ ጋር አለመግባባት ቢፈጠር ወይም በሆነ ምክንያት ጡት ማጥባት ብትከለክለው (ብታቆም)፣ ልጁ በቀላሉ ወደ ወላጅ እናቱ ተመልሶ አስፈላጊውን እንክብካቤ ማግኘት ይችላል፡፡ ህይወቱም ያለምንም እንከን መቀጠል ትችላለች፡፡

5. የማህፀን ኪራይ፣ በትዳር ህይወት ውስጥ በባልና ሚስት መካከል ሌላ ሶስተኛ ሰው ጣልቃ እንዲገባ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፡፡ ባል ወደ ኪራይ እናት የሚሳብበት ክፍተት ይፈጠራል፡፡ ይኸው መጤ ፍልስፍና በምዕራቡ ዓለም ውስጥ ብዙ ቀውሶችን እያመጣ ይገኛል፡፡ አንድ ክስተት እንደ አብነት ብናነሳ፡፡ እንግሊዝ ሀገር ውስጥ ዋናዋ እናት ለኪራይዋ እናት ለመክፈል የተስማማችውን 20 ሺ ፓውንድ የማህፀን ኪራይ ጊዜው ደርሶ ልጇ ከተወለደላት በኋላ አልከፍልም በማለት ጭቅጭቅ አስነስታ ነበር፡፡ የኪራይዋ እናትም ‹‹ብሩን ካላመጣሽ ልጁ የእኔ ነው፣ እውቅና አልሰጥሽ›› ብላ ክስ እንደመሰረተችባት ተሰምቷል፡፡ ይህ ወረርሽኝ በእኛ ሀገር ደረጃ ደግሞ ከዚህ የከፋ ችግሮችን ይዞ እንደማይመጣ ምን ያህል እርግጠኞች ነን? ስለዚህ ልብ ያለው ልብ ይበል ነው ነገሩ፡፡

የወንድ ዘር (ስፐርም) ልገሳ

ስለማህፀን ኪራይ ካነሳን ዘንዳ፣ ጉዳዩ ተቀራራቢነት ስላለው የወንድ ዘር (ስፐርም) ልገሳን በተመለከተ ትንሽ ማለት ወደድን፡፡ እርስዎ እስካሁን ከሰሟቸው ልገሳዎች ‹‹የደም፣ የልብ፣ የኩላሊት፣ የዓይን ልገሳ ወዘተ…›› ባለፈ ወንዶች ፍትወታቸውን በመለገስ ላይ ናቸው፡፡ በዚህ ሂደት ደግሞ አንድ ‹‹ቸር›› የሆነ ወንድ፣ በዚህ ልገሳ ከተሰማራ ስለማንነታቸውና ስለዚህች ምድር ዕጣ ፈንታቸው የማይጨነቅላቸውን ጭራሹንም የማያውቃቸውን የትየለሌ ልጆች ሊያፈራ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡
ይህ የማስተዋል አቅሙ ላልከዳው ሰው፣ እጅግ ከባድና ዘግናኝ በመሆኑ ለመስማት እንኳን የሚከብድ ጉዳይ ነው፡፡ ኢስላም በተለይ ወንድ እንደ አባት ለልጆቹ፣ የምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ዓለም ሁለንተናዊ ዕጣ ፈንታቸው የሚበጃቸውን የማመላከት፣ የመንከባከብና መሰል ኃላፊነቶች አስረክቦታል፡፡ ወንዱ የአባትነት ሚናውን ለማይወጣበት ይህ አይነት የዘር (ስፐርም) ልገሳ ክልክል ነው፡፡

Health: ለባለትዳሮች 10 በሽታን መከላከያ ምክሮች!!

$
0
0

በጋብቻ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች፣ በላጤነት ከሚኖሩት ይልቅ ረዥም ዕድሜ የመኖር ዕድል እንዳላቸው ነው ፊትነስ መጽሔት የምርምር ውጤቶችን ዋቢ የሚያደርገው፡፡ ‹ከአንድ ብርቱ…› እንደሚባለው፣ ጥምረቱ የሚያመጣቸው መተሳሰቦች፣ ጫና እና ኃላፊነት በመሰረታዊነት የሰዎችን ደስታና ዕድሜን ይቀጥላል ነው የጥናቱ ሐሳብ፡፡ ትዳር በጥቅሞቹ ብዛት የተከበበ ቢሆንም፣ በጤና እና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ እንቅፋት ከሚሆኑ ችግሮች ሙሉ ለሙሉ ነፃ ሊሆን አይችልም ይላሉ ባለሙያዎቹ፡፡

fast food

በአሁኑ ወቅት የበርካቶቹ ባለትዳሮች፣ የጤና ችግሮች መንስኤ ተብሎ የሚቀመጠው ከልክ ያለፈ ውፍረት ሲሆን፣ ከዓለም አቀፍ ጦርነቶች ባልተናነሰ መልኩ የሰው ልጅ ከፍተኛው ስጋት ሆኗል፡፡ ውፍረት ለደም ግፊት፣ ለስኳር፣ ለልብ ህመም፣ እና ለሌሎች በሽታዎች ጠንቅ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ግን ትዳርን ከዚህ የጤና ጠንቅ ጋር በቀጥታ ምን አገናኘው? የሚል ጥያቄ ሊቀርብ ይችላል፣ የተለያዩ ጥናቶች የሰዎችን አመጋገብ ከትዳር በፊትና በትዳር ውስጥ ያለውን ልዩነት ፈትሸዋል፡፡ በትንሹ ለሁለት ዓመታት በጋብቻ ውስጥ የቆዩ ጥንዶች፣ ከጋብቻ ውጪ ተጋላጭነታቸው የሰፋ ነው፡፡ በ20ዎቹ ዕድሜ ክልል ውስጥ ያለች አንዲት ሴት፣ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት በትዳር ላይ ስትቆይ በአማካኝ 24 ፓውንድ ክብደት ታከማቻለች ይላል 2012 ላይ በጉዳዩ ላይ የወጣው ጥናት፡፡

ትዳር እንዴት ከልክ ላለፈ ውፍረት ያጋልጣል?

ትዳር ለውፍረት ምክንያት የሚሆንባቸው ምክንያቶች በርካታ ናቸው፡፡ የትዳር አጋሮች ካላገቡት አንፃር ብዙ ጊዜ ምግቦቻቸውን በጋራ ይመገባሉ፡፡ ለመመገብ ረዥም ጊዜ መጠቀማቸው ሌላው የሚጠበቅ ተግባር ነው፡፡ ይሄ ለምሳሌ ያለምንም መጣደፍ ቴሌቪዥን በመመልከት፣ ሞባይል በመነካካት፣ በማውራት እንዲሁም ከሌሎች ተግባራት ጎን ለጎን መመገባቸው፣ አውቀውትም ሆነ ሳያውቁት ከፍተኛ የምግብ ክምችት ወደ ሰውነታቸው እንዲያስገቡ ሊያደርጋቸው ይችላል፡፡

በሌላ በኩል በቤት ውስጥ የሚሰናዱ ምግቦች ስብ እና ሌሎች ውፍረት አመንጪ ንጥረ ነገሮችን በሰፊው ይከተትባቸዋለ፡፡ በዚህም የቤተሰቡ አባላት ከፍተኛ ክብደት ለማከማቸት ብዙ መመገብ እንኳን ላያስፈልጋቸው ይችላል፡፡

በጋራ መመገብ ትዳር ለሚያመጣው ከልክ ያለፈ ውፍረት ሌላው መንስኤ ነው፡፡ የትዳር ተጣማሪዎች በቤት ውስጥ ለመመገብ እስከቀረቡ ድረስ በጋራ መመገባቸው በተለይ እንደኛ ባሉ ሀገራት የተለመደ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ በርታ በርቺ በመባባል የቀረበውን ምግብ በጋራ ለማጥቃት ይረዳል፡፡ ሁኔታው በተለይ የአፒታይት ችግርና የምግብ ጠበኝነት ላለበት ሰው መልካም ሲሆን፣ ወትሮም የምግብ ነገር ለማይሆንላቸው ደግሞ ይዞባቸው የሚመጣው ጣጣ ሊኖር እንደሚችል ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ አዎ ውፍረት ከጤና ጠንቅነቱ ባለፈ ብዙ የተደከመበትንና ዕድሜ የተከፈለበትን ትዳር ይረብሻል እና በእርግጥም መፍትሄ ያሻዋል፡፡

– በተለይ ያላገቡ ሴቶች አዘውትረው የሚለብሱት ሱሪ ጠበብ ማለት ሲጀመር ቶሎ መፍትሄ የመሰላቸውን ተግባር በሙሉ ለመፈፀም ወደኋላ አይሉም፡፡ አመጋገብን መግራት ልምምዶችን ማድረግ ደግሞ መሰረታዊ እርምጃዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሴቶች ወደ ትዳር ሲገቡ እና በተመሳሳይ በውፍረት ሳቢያ ሱሪያቸው የመጥበብ ምልክት ቢያሳያቸው ሌላ መግዛት ነው ቀዳሚው ምርጫቸው፡፡

– ባለትዳሮች ከላጤዎቹ አንፃር በህይወታቸው የተረጋጉ ናቸው፡፡ ይሄ የሚመጣው በተለይ የምወደው የምወዳት ቀሪውን ህይወቴን አብሮኝ የሚኖር ሰው አግኝቻለሁ ከሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ ይሄ ታዲያ አንዳንዶች ራስን መጠበቅ ተጨማሪ ሥራ አድርገው እንዲመለከቱ ያደርጋል፡፡ ውፍረት አመንጪ ሁኔታዎችንም ቤታቸው ውስጥ መፍጠር ይጀምራሉ፡፡ የፊትነስ ባለሙያዎች ችግሩ በሴቶች ላይ ይበረታል ነው የሚሉት፡፡

በትዳር ውስጥ ከልክ ያለፉ ውፍረቶችን መከላከያ 10 ውጤታማ መንገዶች

1. በራስ ስኬት እና ለውጥ ላይ መጀመሪያ ትኩረት ማድረግ

በትዳር አጋርህ ወይም አጋርሽ መጥፎ ልማዶች (በአመጋገብ እና በእንቅስቃሴዎች) በምንም መንገድ መዘናጋት አያስፈልግም፡፡ የትዳር አጋርህን ወይም አጋርሽን የምታነሳሽትና ወደ ውፍረት መቀነሻ ተግባሮች የምናመጣበት ብቸኛው አማራጭ የሚሆነው ምሳሌ ሆኖ መገኘት ነው፡፡

2. የውስጥ ማንነት እንጂ አካላዊ ገፅታ

ለእኔ ቦታ የለውም የሚለውን አመለካከት ማራቅ ያስፈልጋል፡፡ ቀደም ሲል ወደ ትዳር ሲገባ ምክንያት የነበረው ውበት በግንኙነት ሂደት ውስጥ ሲጠፋ ድብርት፣ ስሜት ማጣትና አለመግባባት ይከተላል፡፡ ስለዚህ በግንኙነት ውስጥ ሁሉም ነገር ወሳኝ ናቸውና ግዴለሽነትን በቅድሚያ ማስወገድ አለብን ነው ባለሙያዎች የሚሉት፡፡

3. ከትዳር አጋር ጋር ሰፊ ጊዜን በምግብ ላይ አለማሳለፍ

ከሁለቱም የሚመጡ የእንቅስቃሴ ግብዣዎች ሩጫና የዳንስ ክፍለ ጊዜ መፈቃቀሩ ዕድሜ እንዲኖረው ያደርጋል የምትለው ጄኔፌር ኮኸን ነች፡፡ የተስተካከለ አካላዊ ቁመና በትዳር ውስጥ የወሲብ ህይወትን፣ በራስ መተማመንን እንዲሁም ኃይልን በማቆየት ረገድ ቀዳሚው ባለድርሻ ነው፡፡

4. ለራስ ጊዜ መስጠት፡- የቅርብ ጊዜ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ ጭንቀት በሰውነት ላይ ቀጥተኛ የቅርፅ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል፡፡ አድሬናሊን እና ኮንቲሶል የሚባሉ ሆርሞኖች፣ በሰውነት ውስጥ እንዲሰራጩ በማድረግም፣ የደም ግፊት ከማስተካከል ባለፈ ልብ ከመደበኛው መጠንም በላይ በፍጥነት እንዲመታ በማድረግ፣ ራሳችንን ለአደጋ እናጋልጣለን፡፡ ስለዚህ በትዳራችን ውስጥለጭንቀትና ለአለመረጋጋት የሚያጋልጡንን ምክንያቶች መቅረፍ ያስፈልጋል፡፡

5. ዮጋ፡- ከፍተኛ ኃይል፣ ጥሩ ቅርፅ፣ ተጣጣፊነት፣ የተሻለ መንፈስና ዝቅተኛ ጭንቀት እንዲኖረን የሚረዳንን ዮጋን ማዘውተር ይመከራል፡፡ ባለሙያዎች ዮጋን ስንሰራ በአዕምሯችንና በሰውነታችን መካከል ትስስር እንዲኖር ያደረጋል ነው የሚሉት፡፡ በተቻለ መጠን እንቅስቃሴውን አሁንም ከትዳር አጋራችን ጋር በጋራ እንድንሰራ ይመከራል፡፡ ዮጋ የውስጥ እና የውጭ ሰውነታችን በአካል ደረጃ የሚያሰራ በመሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል፡፡

6. ፍራፍራችን ማዘውተር፡- የሮማን ፍሬ ጁስ እጅግ ዝቅተኛ የኮሌስትሮል መጠን ያለውና የደም ግፊትን በመቀነስ ትልቅ ጥቅም ሲያስገኝ፣ ውፍረትን ደግሞ ይቆጣጠርልናል፡፡ ሌሎች ፍራፍሬዎችንም በአመጋገብ ዝርዝራችን ውስጥ ማካተት ያስፈልገናል፡፡

7. አረንጓዴ ሻይን ማዘውተር

የዚህ ቅጠል የጤና ጥቅሞች በየጊዜው እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡ አረንጓዴ ሻይ ለከፍተኛ ውፍረት መንስኤ የሆነውን ኮሌስትሮልን ከመከላከል ባለፈ የተለያዩ የካንሰር በሽታዎችን ይታገላል፡፡

8. እንደ ሌሎች የሥራና የኑሮ ቀጠሮዎች ሁሉ ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ በቀላሉ የማይሰረዙ ፕሮግራሞችን መቅረፅ ነው የሚያስፈልገው፡፡ ባለሙያዎች ዓርብ ምሽትና ቅዳሜ ጠዋትን በተለይ ባለትዳሮች ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ ምርጫቸው ቢያደርጓቸው የተሻ ነው ይላሉ፡፡

9. ለትዳር አጋር ውለታ መዋል፡- የውፍረት ችግር የሌለባቸው ሰዎች ባሎች ወይም ሚስቶች በአንፃሩ ከውፍረት ጋር የሚኖሩ አጋሮቻቸውን መርዳት አለባቸው ነው የባለሙያዎች ምክር፡፡ በተለይ ትዳር ለዘለቄታው ለማቆየት ራስን በወዳጅ ጫማ ውስጥ ከቶ ስሜቶቻቸውን በመጋራት ከዛም የመፍትሄ አካል በመሆን ወደ መደበኛ ሰውነት ቅርፅ ለማምጣት መረዳት ያስፈልጋል፡፡

10 የትዳር ተጣማሪዎች ከልክ ላለፈ ውፍረት የሚያጋልጡ እርምጃዎችን ለመወሰን አንዱ በአንዱ ላይ ጫና እንደሚያሳድሩት ሁሉ ጤናማ አመጋገብ በጎጇቸው ውስጥ እንዲኖር እና የእንቅስቃሴ ልማድም የዘወትር ተግባራቸው እንዲሆን መተጋገዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡

Viewing all 281 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>